ልጥፎች

ከዲሴምበር, 2021 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ምርኩዝም ኩራዝም የሆነ ልጃቸውን በአደባባይ የተነጠቁ እናት ልጄ ጥራኝ ይላሉ

ምስል
አንድ ልጃቸው በአሸባሪው ህወሓት ሴት ታጣቂ በአደባባይ የተገደለባቸው አይነ ስውሯ እናት ወራሪው ቡድን ያለጧሪና ቀባሪ አስቀረኝ ይላሉ፡፡ ዞኑ ሰሜን ወሎ፣ ከተማው ደግሞ ላልይበላ ነው። በዕለተ እሁድ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት አካባቢ፤ መልካሙ በቀለ፣ ከአቅመ ደካማ እናቱ ጋር ቤት ያፈራውን ሊቀምስ አብሯቸው ተቀምጧል። ቁርሱን አፉ ላይ ጣል እንዳደረገም አፍታም አልቆየም፤ ጠደፍ ብሎ ወጣ። መለስ እንደሚልና እንደሚያያቸው ያውቁ ስለነበር እናቱ ወይዘሮ ቦሰና ገላው፣ ቶሎ አለመመለሱን አልወደዱትም፤ በደከመና ቡዝዝ ባለ አይናቸው ፍዝዝ ብለው በር በሩን ያዩ ጀመር። ጧሪና ቀባሪ ልጃቸው ግን አልከሰት አላቸው። ከደሳሳ ጎጇቸው ደጃፍ ላይ ኩርምት ብለው ሳይነሱ የምሳ ሰዓት አለፈ። ተስፋ ሳይቆርጡ አንዴ ወደ ደሳሳ ጎጇቸው ገባ ይሉና ብዙም ሳይቆዩ ደግሞ ካዘነበለው የግቢያቸው አጥር ወጣ ብለው ያለወትሯቸው የናፈቁትን የልጃቸውን አይን ለማየት ተመኙ። የእናትነት አንጀታቸው ሲላወስ አንዳች የተፈጠረ ክፉ ነገር ይኖር ይሆን ሲሉም ክፉኛ ተጨንቀው ማሰብ ጀመሩ። የፈሩት ይወርሳል፤ የጠሉት ይደርሳል እንዲሉ፤ ጀምበር ከመጥለቋ በፊት 11 ሰዓት ላይ ጆሯቸውን የሚሰቀጥጥ፣ አንጀታቸውን ይበልጥ የሚያንሰፈስፍ፣ ቆሽታቸውን የሚያደብን መጥፎ ዜና ሰሙ። አይን አይኑን የሚያዩትና አይናቸው የሆነ ልጃቸው ከቤት እንደወጣ ወዲያው ሦስት ሰዓት ላይ አሸባሪው የሕወሓት ኃይል አደባባይ ላይ ረሽኖታል ተባሉ። ይህን ለእናቱ ምርኩዝም ኩራዝም የሆነ ልጅ ከተደፋበት ማንም እንዳያነሳው ተብሎ በአሸባሪ ቡድኑ ትዕዛዝ በመሰጠቱ፣ ማንም ደፍሮ ሊያነሳው አልቻለም። ይህም በመሆኑ እስከ ቀኑ 11 ሰዓት ድረስ በተደፋበት ቦታ ይቆያል። ከአሁን አሁን ይመጣልኛል ብለው ከጎጇቸው በር ላይ አይናቸውን ክርትት ክርትት ሲያደርጉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በድል የታጀበውን የመጀመሪያ ምእራፍ ቆይታቸውን አጠናቀው ለተወሰነ ጊዜ ወደ ቢሮ ተመለሱ

ምስል
  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በድል የታጀበውን የመጀመሪያውን ምእራፍ ቆይታቸውን አጠናቀው ለተወሰነ ጊዜ ወደ ቢሮ መመለሳቸውን ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ባወጡት መግለጫ፥ ዛሬም ሆነ ወደፊት ጠላቶቻችን ጉልበታቸው ዝሎ፣ የጥላቻና የጠበኝነትን መንገድ ጥለው፣ የፍቅርና የሰላምን መንገድ እስኪመርጡ ትግላችን ይቀጥላል ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል። “በድል የታጀበው የመጀመሪያው ምእራፍ” ውድ የሀገሬ ልጆች፣ የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ወዳጆች፣ ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ ትከበራለች፤ ትታፈራለች። ኢትዮጵያን መገዳደር ይሞከር ይሆናል። ተገዳድሮ ማሸነፍ ግን ትናንትም አልተቻለም፤ ዛሬም አይሆንም፤ ነገም አይቻልም። ኢትዮጵያ የሚለው ስም ሁሌም ከአሸናፊነት ጋር የተያያዘ ነው። ከጥቂት ጊዜያት በፊት ኢትዮጵያን ሊወጋ የተነሳውን ጠላት በጋራ ሆነን እንድንመክት ጦር ግንባር ላይ የያዝነው ቀጠሮ ጠላትን አንገት ሲያስደፋ ኢትዮጵያን ቀና አድርጓታል። ሀገራችን ታፍራና ተከብራ እንድትኖር ለማድረግ በጦር ግንባር እየተከፈለ ያለው መስዕዋትነት የኢትዮጵያን የአሸናፊነት ስም የሚመልስ መሆኑን እያበሰርኩ፣ ያቀረብኩትን ጥሪ ተቀብላችሁ ሕይወታችሁን፣ ጉልበታችሁን፣ ሀብታችሁን፣ ዕውቀታችሁን፣ ጊዜያችሁንና ሞያችሁን ለሠጣችሁ ሁሉ በኢትዮጵያ ስም ላመሰግናችሁ እወዳለሁ። በዚሁ አጋጣሚ፣ የመጀመሪያውን ምእራፍ አጠናቅቄ ለተወሰኑ ጊዜያት ወደ ቢሮ መመለሴን እየገለጽኩ፣ ዛሬም ሆነ ወደፊት ጠላቶቻችን ጉልበታቸው ዝሎ፣ የጥላቻና የጠበኝነትን መንገድ ጥለው፣ የፍቅርና የሰላምን መንገድ እስኪመርጡ ትግላችን ይቀጥላል።የእኛ ፍላጎት ሁሌም ሰላምና ፍቅር ነው። ኢትዮጵያ ሕብረ ብሔራዊ አንድነቷ ተጠብቆ የብልጽግና ጉዞዋ የተቃና እንዲሆን ያለንን ፍላጎት ከጅምሩ አሳውቀን ለተግባ