ልጥፎች

ከ2021 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ምርኩዝም ኩራዝም የሆነ ልጃቸውን በአደባባይ የተነጠቁ እናት ልጄ ጥራኝ ይላሉ

ምስል
አንድ ልጃቸው በአሸባሪው ህወሓት ሴት ታጣቂ በአደባባይ የተገደለባቸው አይነ ስውሯ እናት ወራሪው ቡድን ያለጧሪና ቀባሪ አስቀረኝ ይላሉ፡፡ ዞኑ ሰሜን ወሎ፣ ከተማው ደግሞ ላልይበላ ነው። በዕለተ እሁድ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት አካባቢ፤ መልካሙ በቀለ፣ ከአቅመ ደካማ እናቱ ጋር ቤት ያፈራውን ሊቀምስ አብሯቸው ተቀምጧል። ቁርሱን አፉ ላይ ጣል እንዳደረገም አፍታም አልቆየም፤ ጠደፍ ብሎ ወጣ። መለስ እንደሚልና እንደሚያያቸው ያውቁ ስለነበር እናቱ ወይዘሮ ቦሰና ገላው፣ ቶሎ አለመመለሱን አልወደዱትም፤ በደከመና ቡዝዝ ባለ አይናቸው ፍዝዝ ብለው በር በሩን ያዩ ጀመር። ጧሪና ቀባሪ ልጃቸው ግን አልከሰት አላቸው። ከደሳሳ ጎጇቸው ደጃፍ ላይ ኩርምት ብለው ሳይነሱ የምሳ ሰዓት አለፈ። ተስፋ ሳይቆርጡ አንዴ ወደ ደሳሳ ጎጇቸው ገባ ይሉና ብዙም ሳይቆዩ ደግሞ ካዘነበለው የግቢያቸው አጥር ወጣ ብለው ያለወትሯቸው የናፈቁትን የልጃቸውን አይን ለማየት ተመኙ። የእናትነት አንጀታቸው ሲላወስ አንዳች የተፈጠረ ክፉ ነገር ይኖር ይሆን ሲሉም ክፉኛ ተጨንቀው ማሰብ ጀመሩ። የፈሩት ይወርሳል፤ የጠሉት ይደርሳል እንዲሉ፤ ጀምበር ከመጥለቋ በፊት 11 ሰዓት ላይ ጆሯቸውን የሚሰቀጥጥ፣ አንጀታቸውን ይበልጥ የሚያንሰፈስፍ፣ ቆሽታቸውን የሚያደብን መጥፎ ዜና ሰሙ። አይን አይኑን የሚያዩትና አይናቸው የሆነ ልጃቸው ከቤት እንደወጣ ወዲያው ሦስት ሰዓት ላይ አሸባሪው የሕወሓት ኃይል አደባባይ ላይ ረሽኖታል ተባሉ። ይህን ለእናቱ ምርኩዝም ኩራዝም የሆነ ልጅ ከተደፋበት ማንም እንዳያነሳው ተብሎ በአሸባሪ ቡድኑ ትዕዛዝ በመሰጠቱ፣ ማንም ደፍሮ ሊያነሳው አልቻለም። ይህም በመሆኑ እስከ ቀኑ 11 ሰዓት ድረስ በተደፋበት ቦታ ይቆያል። ከአሁን አሁን ይመጣልኛል ብለው ከጎጇቸው በር ላይ አይናቸውን ክርትት ክርትት ሲያደርጉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በድል የታጀበውን የመጀመሪያ ምእራፍ ቆይታቸውን አጠናቀው ለተወሰነ ጊዜ ወደ ቢሮ ተመለሱ

ምስል
  ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በድል የታጀበውን የመጀመሪያውን ምእራፍ ቆይታቸውን አጠናቀው ለተወሰነ ጊዜ ወደ ቢሮ መመለሳቸውን ገለፁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ባወጡት መግለጫ፥ ዛሬም ሆነ ወደፊት ጠላቶቻችን ጉልበታቸው ዝሎ፣ የጥላቻና የጠበኝነትን መንገድ ጥለው፣ የፍቅርና የሰላምን መንገድ እስኪመርጡ ትግላችን ይቀጥላል ብለዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል። “በድል የታጀበው የመጀመሪያው ምእራፍ” ውድ የሀገሬ ልጆች፣ የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ወዳጆች፣ ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ ትከበራለች፤ ትታፈራለች። ኢትዮጵያን መገዳደር ይሞከር ይሆናል። ተገዳድሮ ማሸነፍ ግን ትናንትም አልተቻለም፤ ዛሬም አይሆንም፤ ነገም አይቻልም። ኢትዮጵያ የሚለው ስም ሁሌም ከአሸናፊነት ጋር የተያያዘ ነው። ከጥቂት ጊዜያት በፊት ኢትዮጵያን ሊወጋ የተነሳውን ጠላት በጋራ ሆነን እንድንመክት ጦር ግንባር ላይ የያዝነው ቀጠሮ ጠላትን አንገት ሲያስደፋ ኢትዮጵያን ቀና አድርጓታል። ሀገራችን ታፍራና ተከብራ እንድትኖር ለማድረግ በጦር ግንባር እየተከፈለ ያለው መስዕዋትነት የኢትዮጵያን የአሸናፊነት ስም የሚመልስ መሆኑን እያበሰርኩ፣ ያቀረብኩትን ጥሪ ተቀብላችሁ ሕይወታችሁን፣ ጉልበታችሁን፣ ሀብታችሁን፣ ዕውቀታችሁን፣ ጊዜያችሁንና ሞያችሁን ለሠጣችሁ ሁሉ በኢትዮጵያ ስም ላመሰግናችሁ እወዳለሁ። በዚሁ አጋጣሚ፣ የመጀመሪያውን ምእራፍ አጠናቅቄ ለተወሰኑ ጊዜያት ወደ ቢሮ መመለሴን እየገለጽኩ፣ ዛሬም ሆነ ወደፊት ጠላቶቻችን ጉልበታቸው ዝሎ፣ የጥላቻና የጠበኝነትን መንገድ ጥለው፣ የፍቅርና የሰላምን መንገድ እስኪመርጡ ትግላችን ይቀጥላል።የእኛ ፍላጎት ሁሌም ሰላምና ፍቅር ነው። ኢትዮጵያ ሕብረ ብሔራዊ አንድነቷ ተጠብቆ የብልጽግና ጉዞዋ የተቃና እንዲሆን ያለንን ፍላጎት ከጅምሩ አሳውቀን ለተግባ

የአሸባሪዎቹን ቡድኖች ወያኔና ኦነግ ሸኔን ለሚናፍቁቱ

ምስል
መሃል አገር ተቀምጣችሁ ወያኔ ተመልሶ ይመጣል ብላችሁ ተስፋ በማድረግ ላይ ያላችሁ ወገኖች ተስፋችሁን ቁረጡ አሸባሪዋ ወያኔ የምዕራባዊያን ድጋፍ ቢኖራትም ተመልሳ በመምጣት ኢትዮጵያን የማስተዳደር አቅም በፍፁም የላትም፤አሁን ባዶ ፉከራዋን ብቻ ነው በፕሮፓጋዳ ማሽኖቿ በማሰማት ላይ ያለችው ⵆ የወያኔ ታጣቂዎች ወደ መሃል አገር እየገሰገሱ ነው የሚል የሃሰት መረጃ ስታገኙ ፊታችሁ በተስፋ ሲፈካ፤የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እርምጃ ወሰደ የሚል መረጃ ስታገኙ ደግሞ ፊታችሁ የሚጨፈግግ እንዳላችሁ እየተስተዋለ ነው በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት ውስጥ ዕድል ገጥሟችሁ በመስራት ላይ የምትገኙ የአሸባሪ ቡድን ደጋፊዎች የሚሻላችሁና የሚበጃችሁ በተመደባችሁበት የስራ ዘርፍ ላይ በማትኮር ውጤታማ መሆን ብቻ ነው ከዚህ ውጭ በመንግስት መስሪያ ቤት ውስጥም ሆነ በግል ተቋማት ውስጥ ቦታ ይዘህ/ሽ ወያኔ ተመልሶ ይመጣል ብለህ/ሽ ስትናፍቂ ብትውይ ምንም ጠብ የሚል ነገር ሊኖር አይችልም ይልቅ የሚሻለው በተመደባችሁበት የስራ ዘርፍ ውጤታማ ለመሆን መትጋት ነው፤አለበለዚያ ኢትዮጵያ ውስጥ እጅግ ብዙ ስራ አጥ ወገኖች ስላሉ ያገኛችሁት ዕድል የጊዜ ጉዳይ   ነው እንጂ ሊነጠቅ ይችላል ነገ ሌላ ቀን ነው!በመሃል አገር የአሸባሪውን የሃሰት ፕሮፓጋዳ በመቀበል ስትንቶሶቶሱ ብትውሉ ምንም የሚመጣ ለውጥ የለም ተጠንቀቁ! አንዳንዶቻችሁ ልክ እንደ ቀድሞ ተሰብስባችሁ ወያኔ በምትሰጠው ተልዕኮ ላይ በመወያየት ተልዕኮ ለመፈፀም ያምራችኋል፤እንግዲህ ሲያምራችሁ ይቅር፤አንዳንዶች ደግሞ ባላችሁበት የስራ ዘርፍ ስራን በማጓተት ተፅዕኖ ለመፍጠር ትጥራላችሁ ይህም የአይና አውጣነታችሁን ልክ ያሳያል ኦነግ ሸኔን በመናፈቅ ላይ ያላችሁ ወገኖችም ምንም ተስፋ የምታደርጉት ነገር የለም፤ ኦነግ

Irreechi Ibsaa Aadaafi Seenaa Ummata Oromooti

ምስል
  Irreechi waggaa waggaadhaan dhufa.Baranas kunoo waggaa eeggachuudhaan dhufeera.Irreecha Hora Finfinneefi Arsadii Fulbaana 22 fi 23 bara 2014 ayyaaneeffamuuf baga geesssan! Irreechi hora Finfinnee waggaa 150 booda kabajamuu erga eegalee kan baranaa marsaa sadaffaadha.Irreechi hora Finfinnee marsaa jalqabaafi lammataa yaaddoowwan nagaafi fayyaa utuu jiranuu kabajamuun darbe.Baranas yaaddoowwan kun akka jiran nibeekama. Yaaddoon nagaa tokkummaa Irreeffattoota hundaatiin fala argata.Kanaan duras Oromoon tokko ta’ee socho’uu waan danda’eef sirni Irreechaa utuu mortuun mortuu nagaadhaan kabajamee darbe.Baranas gamtaafi tokkummaa Ummata Oromootiin akkasumas tumsa sabaafi sab-lammootaatiin nagaadhaan kabajamee darba. Waltajjii sirna ayyaana Irreechaa bu’aa siyaasaa galmeessisuuf itti fayyadamuun shira diinoonni Oromoo waggaa waggaadhaan shiran irraa madda.Waggaa darbe Fulbaana 30 booda mootummaan biyya bulchu hinjiru jechuun utuma farrisanii Irreechi hora Finfinneefi Arsadi vaayirasi

አሜሪካ ስለ ኢትየጵያ ያልገባት ነገር…..

ምስል
  አሜሪካ ለአሸባሪው ወያኔ ጁንታ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ ቀጥላለች ⵆ ስለ አሸባሪው ጁንታ መጥፎ ነገር አትናገሩ አስከ ማለትም የደረሰች መሆ ኗን እያየን፤እየሰማን ነው ⵆ አገሪቷ ጁንታው እንደ ድሮው ሁሉ በእጁ ሁሉ በደጁ መስሏት ድጋፍ በማድረግ ላይ የምትገኘው ጥቅሟን መሰረት በማድረግ መሆኑ ግልፅ ነው ⵆ ጁንታው ቀድሞውንም   ኢትዮጵያን የማፍረስ ዕቅድ ስለነበረው ለአመታት ስራውን ሲሰራ ነው የኖረው፤ተግባራዊ ካደረጋቸው ዕቅዶች ወስጥም አንዱ ጀሌዎቹን በተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማት ውስጥ በመሰግሰግ እሱ የማይነካ፤ተሰሚነት ያለውና ጠንካራ እንደሆነ በመዘርዘር በየደረጃው የሚገኙ የአሜሪካ ባስልጣናትን የማሳመን ስራ እንዲሰሩ ማድረግ ነው በዚህ ረገድ የተሳካላቸው እንደሆነ መጠራጠር አያስፈልግም፤አሁን አሜሪካ ያለውን ተጨባጭ እውነታ ባለመረዳት ወይም የቀድሞው ጥቅም የሚቀጥል መስሏት ለጁንታው በጭፍን በማድረግ ላይ ያለችው ድጋፍ ምስክር ነው ወያኔ ለአሜሪካ ባለስልጣናት እየሸጎጠች ያለችው ዶላር ያልቃል ወይም ማለቁ አይቀርም፤ዶላርን ለባለስልጣናት የመሸጎጡ ነገር ከእንግዲህ ሊቀጥል አይችልም፤አሁን ወያኔ ነፍስ ግቢ ነፍስ ውጪ ውስጥ ነው የምትገኘው ለመሞት በማጣጣር ላይ የሚገኘው አሸባሪ ቡድን አሜሪካን እያጃጃለ ነው፤አዲስ አበባ ልገባ ነው እያለ ጁንታው በፕሮፓጋዳው ቢያጃጅላቸው ጥቅማቸውን ስለሚወዱ ተጃጃሉለት አሜሪካ ያልተረዳችው ትልቅ ነገር የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ መሆኑን ነው ⵆ ኢትዮጵያዊያን አንድ ሆነው ቀፎው እንደተነካ የንብ መንጋ መሆናቸውን አሜሪካ በፍፁም አልተረዳችም ⵆ የኢትዮጵያዊያኑን ከብረት የጠነከረ አንድነት ብትረዳ ኖሮ እንዲህ ባልተጃጃለች ነበር ለማንኛውም የጁንታው ነፍስ ልትወጣ ከጫፍ ደርሳለች ⵆ የጁንታው ነፍስ   ሙሉ በ

ትህነግ ደብቃው የቆየችው ዕቅድ ይፋ የወጣበት ሳምንት

ምስል
  አሸባሪዋ ቡድን ትህነግ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የጎነጎነችው የሴራ ዕቅድ ከሰሞኑ ይፋ ወጥቷል ⵆ ከሰማኒያ ገፅ በላይ ነው የተባለው የአሸባሪዋ ጁንታ ቡድን የጥፋት ዕቅድ፤ቡድኗ ለ27 ዓመታት በህቡዕ   ስትፈፅማቸው በቆየችው ተግባ ሯ ላይ የተሰመረቱ ናቸው ማለት ይቻላል ⵆ ወያኔ በቆየታዋ ሁለት መልክ ነበራት፤በግልፅ መድረኮች ላይ የማስመሰል ድራማ ስትሰራ ነው የኖረችው፤በህቡዕ ስታከናውን የኖረችውና በህዝቦች እውነተኛ ትግል ተንገዳግዳ ሙጭጭ ብላ ከቆየችበትና ልትቀጥልበት ከምታስበው ስልጣን ከተወገደች በኋላ በሂደት ተጎልጉለው የወጡ ጎዶቿ ደግሞ የምትታወቅበትን ሁለተኛ መል ኳን ነው ቁልጭ አድርገው ያሳዩት ⵆ ወያኔ እንደ እስስት የመለዋወጥ ባህሪ አላት፤ይህን የመለዋወጥ ባህሪ እንዳላት ጥቅማቸውን መሰረት አድርገው   እርስዋን ተስፋ በማድረግ ከሚናውዙት በስተቀር የወያኔን አስስታዊ ባህሪ ሁሉም ወገን ተረድቷል፤በተለይም እውነተኛ ኢትዮጵያዊያን ወያኔ በህቡዕ ስትፈፅም የኖረችውን ወንጀሎች ከተረዱ በኋላ በቁጭት ውስጥ እንዳሉ ይታወቃል ⵆ “ጅብ ከማይታወቅበት አገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ”ይላል እንዲሉ ትህነግም ስፍር ቁጥር የሌለው ሴራዋ በኢትዮጵያ ህዝብ ያልታወቀባት መስሏት እንዲሁም የውጭ ጌቶቿን ተስፋ በማድረግ ወደ ለመደችው ስልጣኗ ለመመለስ ወይም ኢትዮጵያን አፍርሳ ትግራይን አገር ለማድረግ በመፍጭረጨር ላይ ብትገኝም አስከ ወዲያኛው የመጥፋት ጊዜዋ ቀርቧል ⵆ ኢትዮጵያን ለማፍረስ በሴረኛዋ ወያኔ ታስቦበት የተያዘው ዕቅድ እስከ አሁን በነበረው መፍጨርጨር ከፊሉ ተግባራዊ ቢሆንም አሁን ባለው ሁኔታ ኢትዮጵያ ከመፍረስ አደጋ ሙሉ በሙሉ ተርፋለች ⵆ የሴረኛዋ ወያኔ ዕቅድ ከግቡ ሳይደርስ እንዲከሽፍ ሁሉም የኢትዮጵያ ልጆች በአንድነት ቆመዋል ⵆ አሁን ወያኔ

Artiistoonni keenya galatoomaa!

ምስል
  (Finfinnee-Fulbaana 04/01/2014) Tibbana walleewwan   adda addaa duula Raayyaan Ittisa biyyaafi humnoonni tasgabbii gara garaa eegalan jajjabeessaniifi onnachiisan Afaan Oromoo dabalatee afaanota gara garaatiin ba’uun qilleensarra oolaa jiru.Qabiyyeen sirboota ba’an hundaa baay’ee gaariidha.Kan yeroo gabaabaa keessati qophaa’ee dhiyaate hinfakkaatu. Qabiyyeen hundumaatuu Raayyaa ittisa biyyaafi humnoota tasgabbii hunda kan onnachiisan,lammiiwwan hundas kan kakaasan waan ta’eef Artiistoota Oromoo dabalatee arstiistoonni sabaafi sab-lammootaa milkaa’inaan hojii haarawaa kana kutannoodhaan yeroo gabaabaa keessatti hojjetan galateeffachuun barbaachisaadha. Akkana kunoo waamicha biyyaatiif awwaachuun! Ijoolleen Itiyoophiyaa dameewwan hojii adda addaa irratti bobba’an waamicha biyyasaanii dhaggeeffachuudhaan deebii qabatamaa ta’e kennaa jiru.Qeerroofi Qarreen waamicha biyyaatiif awwaachuudhaan caasaa raayyaa ittisa biyyaatti makamaniiru,makamaas jiru. Lammiin hundi tokkummaa lelis