ልጥፎች

ከኤፕሪል, 2017 ልጥፎች በማሳየት ላይ

በአዲሱ የኦሮሚያ አመራር የጥገኞቹ ስጋት ለምን?

ምስል
የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ለማ መገርሳ በ2009 ዓ.ም መጀመሪያ ወራት ላይ ወደ ኃላፊነት ከመጡ ወዲህ በአጠቃላይ የኦሮሞ ሕዝብ በተለይም የኦሮሚያ ወጣቶች ኢኮኖሚዊ ተጠቃሚነት ያለምንም ማቅማማት እንዲረጋገጥ ብርቱ ጥረት በማድረግ የሚታይና የሚጨበጥ ለውጥ በማስመዝገብ ላይ ይገኛሉ ርዕሰ መስተዳድሩ  ገና በመጀመሪያው ዓመት የስልጣን ዘመናቸው በማስመዝገብ ላይ ያሉት ለውጥ ቀጣይና የሰፊውን የኦሮሞ ሕዝብ ድጋፍ በማግኘት ተጠናክሮ መቀጠል የሚችል መሆኑን ብዙዎች ከወዲሁ ገምተዋል፤ መገመት ብቻ  ሳይሆን በርዕሰ መስተዳድሩ ቁርጠኛ አካሄድ በልበ ሙሉነት ተማምነዋል ማለትም ይቻላል። አቶ ለማ መገርሳ በክልሉ ይበል የሚያሰኝ ለውጥ በማስመዝገብ ላይ የሚገኙት በሰፊው የኦሮሞ ሕዝብ ድጋፍና በአካባቢያቸው ካሉ አመራሮች በሚያገኙት እገዛ መሆኑ ግልፅ ነው የርዕሰ መስተዳድሩ ቁርጠኝነት ምንም ያህል ጠንካራ ቢሆን በኦሮሞ ሕዝብና በአካባቢያቸው ከሚገኙ አመራሮች የተሟላ ድጋፍ ስላላቸው እንደሆነ ሊታወቅ ይገባል፤ከሶስት ሚሊየን በላይ የሆነው ትክክለኛ የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት አባላትና ትክክለኛ የእህት ድርጅቶች አባላትም ከክቡር አቶ ለማ መገርሳ ጎን መሆናቸው ሊዘነጋ አይገባም! ክቡር አቶ ለማ መገርሳ በክልሉ በየዘርፉ የሚታዩ ፖለቲካዊ፤ማህበራዊና ኢኮኖሚዊ ችግሮች ደረጃ በደረጃ አስተማማኝ መፍትሄ እንዲያገኙ የሚሰሩ እንዲሁም የኦሮሚያን ሕዝብ  በብቃት መምራት የሚችሉና የኦሮሞ ሕዝብ ለዘመናት ለአገር አንድነትና ዕድገት ሲያበረክት የኖረውን የማይተካ አስተዋፅኦ በማስተባበር ማስቀጠል የሚችሉ ብቁ አመራር ናቸው። ይህን ሃቅ በመካድ የክቡር አቶ ለማ መገርሳንና በአቅራቢያቸው የሚገኙ አመራሮችን መልካም ጥረት ለማጉደፍ ከቻሉም

የኦሮሚያና የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልሎች በ1997 የተካሄደውን ህዝበ ውሳኔ ሙሉ በሙሉ ለመተግበር ተስማሙ

ምስል
የኦሮሚያ እና የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልሎች በ1997 የተካሄደውን ህዝበ ውሳኔ ሙሉ በሙሉ ለመተግበር ተስማሙ። የሁለቱ ክልሎቹ ርዕሰ መስተዳደሮች በፈረሙት ስምምነት ህዝበ ውሳኔውን መሰረተ በማድረግ የአስተዳደር ወሰን ያልተካለለባቸው አካባቢዎችን ለማካለል ተስማምተዋል። በተጨማሪም ሁለቱ ክልሎች ዛሬ በተፈራረሙት ሰነድ የ1997 ዓ.ም ህዝበ ውሳኔን ተከትሎ የተደረሰውን የአስተዳደራዊ የወሰን ስምምነት ተቀብለው ተግባራዊ ለማድረግ ከስምምነት ደርሰዋል። ሁለቱም ክልሎች የስምምነቱን ሰነድ በተፈራረሙ በሶስት ወራት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ አስተዳደራዊ ወሰኑን ለህዝብ ይፋ በማድረግ ማጠቃለል ላይም ተስማምተዋል። እንዲሁም አጎራባች ዞኖች ወረዳዎች እና ቀበሌዎችን በልማት እና መልካም አስተዳደር ማስተሳሰር የሚለውም የስምምነቱ ሰነድ አካል ነው። በሁለቱ ክልል መንግስታት በኩል የውሳኔውን አፈፃፀም የሚያስተጓጉሉ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ በጋራ መስራት፤ ከስምምነቱ በኋላ አጎራባች አካባቢዎች ለግጭት መንስኤ የሚሆኑ ኬላዎችን ማስወገድ የሚሉትም በስምምነቱ ላይ ተካተዋል። በህዝበ ውሳኔው እና አስተዳደራዊ ወሰን የማካለል ስምምነት መሰረት በሁለቱ ክልሎች የሚኖሩ ማህበረሰቦች ህገ መንግስታዊ መብታቸውን መጠበቅ የሚለ የስምምነቱ አካል ነው። አስተዳደራዊ ወሰን ከማካለል ስምምነት በኋላ በማናቸውም መልኩ ማህበረሰቦችን አለማፈናቀል፤ በመኖሪያ አካባቢያቸው ይኖራሉ የሚለው እና ከአስተዳደራዊ ወሰን ማካለል ጋር ተያይዞ የታሰሩ ሰዎች ካሉ እንዲለቀቁም ማድረግም በስምምነቱ ውስጥ ተካቷል። የፌደራል እና አርብቶ አደር ልማት ጉዳዮች ሚንስትሩ አቶ ካሳ ተክለብርሀን ሰነዱ በተለያዩ ጊዜያት በተፈጠሩ ግጭቶች ህይወታቸውን ያጡ ዜጎች የቃል ኪዳን ሰነድ ነው ብ

Jeeqamsichaan lubbuu lammiiwwan 669tu darbe

ምስል
Jeeqamsi waggaa darbe Naannoo Oromiyaa,Amaaraafi Ummattoota kibbaa iddoowwan gara garaatti mudate lubbuu marartuu lammiiwwan keenya 669 galaafateera. Komishinarri komishinii mirga Namoomaa Itiyoophiyaa Dr.Addisuu Gabraigzaabeer kaleessa gabaasa komishiinichi yeroo hedduu fudhatee qindeessaa ture mana maree bakka bu'oota ummataatiif dhiyeessaniiru. # Oromia # Ethiopia # Oromiyaa Kan darbe irraa baratee rakkoon lammataa akka hin mudanne taasisuu kan danda'u sirna heera mootummaa ke enya hordofuudhaan kan hojjetu akka ta'e hubachuun barbaachisaadha. Gabaasa komishinarichi dhiyeessan irraa hubachuun akka danda'ametti gabaasichi gartummaa irraa bilisa ta'uudhaan kan qophaa'edha. Akka gabaasichaan eerametti iddoo tokko tokkotti qaamoleen tarkaanfiin walsimaa hintaane akka fudhatamu taasisan seeraan gaafatamu. Lammiiwwan dhibba jahaa ol sababa jeeqamsaatiin Naannolee gara garaatti lubbuunsaanii darbe keessaa dhibba 4 kan Caalan jiraattota Naannoo

የስነ ዜጋና ስነ ምግባር ትምህርት የሚፈለገውን ውጤት አለማምጣቱን አንድ ጥናት አመለከተ

ምስል
የስነ ዜጋና ስነ ምግባር ትምህርት የሚፈለገውን ውጤት አለማምጣቱን አንድ ጥናት አመለከተ። የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር "በትምህርት ተቋማት የስነ ዜጋና ስነ ምግባር ግንባታና ዴሞክራሲያዊነት፣ ተግዳሮቶችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች" በሚል ርዕስ የተካሄደ ጥናት ዛሬ ውይይት ተደርጎበታል። የጥናትና ምርምር ማዕከሉ ባካሄደው ጥናት ግኝት መሰረት፥ ከአምስተኛ ክፍል ጀምሮ ሲሰጥ የቆየው የስነ ዜጋና ስነ ምግባር ትምህርት በአመራር ድክመት የሚጠበቅውን ውጤት አላስገኘም ተብሏል። የትምህርት ዘርፉ የተፈለገውን ውጤት እንዲያመጣ ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር መምራት አለመቻሉን ያመላከተው ጥናቱ፥ የመማሪያ መፅሐፉ ይዘት የተደጋገመ መሆን፣ አቀራረቡ ከዓላማው ጋር መቃረኑ እና የትምህርቱ መርሀ ግብር የሚመራበት በቂ አደረጃጀትና አሰራር አለመኖርን በቁልፍ ችግርነት አንስቷል። የተማሪዎችን ስነ ምግባር ለመከታተል የሚያስችል አሰራርና አደረጃጀት እስካሁን አለመዘርጋቱንም ጥናቱ ይፋ አድርጓል። ከዚህ በተጨማሪም የስነ ምግባር ትምህርትን ጉዳይ የመምህራን ኃላፊነት ብቻ አድርጎ መቁጠር፣ በመምህራን፣ በተማሪዎችና ወላጆች መካከል ያለው ግንኙነት የላላ መሆኑም ተገልጿል። የስነ ዜጋና ስነ ምግባር አስተማሪዎች የብቃትና የአቀጣጠር ችግር መኖሩ በጥናቱ የተጠቆመ ሲሆን፥ ትምህርቱን ለሚሰጡ መምህራን ከፍተኛ ትኩረት መስጠትና ማብቃት እንደሚያስፈልግም ነው የተመለከተው። የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይ ፀሀዬ፥ ለትምህርቱ ለውጥ አለማምጣት የአመራሩ ድክመት ተጠቃሽ መሆኑን ተናግረዋል። አቶ በረከት ስምዖንም ችግሩ የአመራር መሆኑን ጠቅሰው፥ የማስተካከል ፈጣን እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል ብለዋል።

Dhimma albuudaa galtee simintoo !!

ምስል
“Warshaaleen simintoo bakkeewwan albuudaa akka gadi lakkisan ajajaman mootummaa naannoo oromiyaa waliin maree taasisuudhaan qabiyyeessanii kabachiifatan” jechuudhaan gaazexaan riippoorter gaafa guyyaa 6/8/2009 gabaabsni dhiyeesse dogoggora ta’uusaa ibsuudhaan, dhimmicha caalmaatti ifa gochuudhaaf balballoomii dabalataa qabannee dhiyaanneerra. Galteewwan simintoof kan oolan bakkeewwan albuudaa armaan dura warshaaleedhaan qabamanii turan   mootumman naannoo oromiyaa tarkaanfiiwwan bu’uraa lama irratti fudhateera. Inni jalqabaa warshaa simintoo osoo hin qabaanne karaa addaddaatiin hojichaafi bakka albuudoota kanneennii qabatanii kan turaniifi galtee tokkollee osoo itti hin dabalin Ashawaa fi Puumiisii haranii abbootii qabeenyaa gurgurataa turan irratti tarkaanfii fudhatameen damee kana keessaa akka bahaniifi qabeenyaa horataniin invastimantii biraatti cehanii akka dorgoman taasifameera. Tarkaanfiin inni lammataa warshaaleen simintoo naannoo keenyatti argaman oomsiha simintoo kees

የክልሉ መንግስት የሪፖረተር ጋዜጣን ዘገባ ሀሰተኛ ነው በማለት ኮነነ በህግም እጠይቃለሁ ብሏል

ምስል
የክልሉ መንግስት የሪፖረተር ጋዜጣን ዘገባ ሀሰተኛ ነው በማለት ኮነነ በህግም እጠይቃለሁ ብሏል በአቶ አማረ አረጋዊ ባለቤትነት የተያዘው የሪፖረተር ጋዜጣ ሚያዝያ 6/2009 ባወጣው ዕትም “ የማዕድን ቦታ እንዲያስረክቡ የታዘዙ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ከኦሮሚያ ጋር በመደራደር ይዞታቸውን አስከበሩ ” በሚል ርዕስ ያወጣውን ዘገባ የክልሉ መንግስት የኮሙኒክሽን ጉዳዮች ቢሮ በአፅንኦት ኮነነ ጋዜጣው በሃሰት ያወጣውን ዘገባ አስተባብሎ የክልሉን መንግስት ይቅርታ የማይጠይቅ ከሆነ በሕግ ለመጠየቅ እንደሚገደድም ቢሮው አስታቋል የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የክልሉን ወጣቶች በሚጎዳ መልኩ ከየትኛውም አካል ጋር እንዳልተወያየና ወደፊትም ለመወያየት ፍላጎትና እምነት እንደሌለው ጠቁሟል ከሲሚንቶ ፋብሪካዎች ጋር በተያያዘ የክልሉን ወጣቶች ተጠቃሚነት አስመልክቶ ህብረተሰቡ የተሟላ ግንዛቤ እንዲኖረው በቀጣይ በኦሮሚያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት ተከታታይ ዘገባዎች እንደሚቀርቡም ተነሯል የሪፖርተር ጋዜጣ አሳትሞ አሰራጭቷል የተባለው ዘገባ ቀጥሎ ያለው ነው ያንብቡ፡http://ethiopianreporter.com/content/%E1%8B%A8%E1%88%9B%E1%8B%95%E1%8B%B5%E1%8A%95-%E1%89%A6%E1%89%B3-%E1%8A%A5%E1%8A%95%E1%8B%B2%E1%8B%AB%E1%88%B5%E1%88%A8%E1%8A%AD%E1%89%A1-%E1%8B%A8%E1%89%B3%E1%8B%98%E1%8B%99-%E1%8B%A8%E1%88%B2%E1%88%9A%E1%8A%95%E1%89%B6-%E1%8D%8B%E1%89%A5%E1%88%AA%E1%8A%AB%E1%8B%8E%E1%89%BD-%E1%8A%A8%E1%8A%A6%E1%88%AE%E1%88%9A%E1%8B%AB-%E1%8C%8

ይፋዊ ጉብኝቶችን አስመልክቶ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃልአቃባይ አቶ መለስ አለም የተሰጠ ማብራሪያ

ምስል
በክቡር ጠቅላይ ሚ / ር ኃይለማሪያም ደሳለኝ እና በውጭ ጉዳይ ሚ / ር ክቡር ዶ / ር ወርቅነህ ገበየሁ የተደረጉ ይፋዊ ጉብኝቶችን አስመልክቶ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃልአቃባይ አቶ መለስ አለም የተሰጠ ማብራሪያ መግቢያ በአፍሪካ ቀንድ የሚገኙትና አገራችን በረጅም ጊዜ ታሪክ የተሳሰረቻቸው ጎረቤት አገሮች ማለትም ኬንያ፣ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ጅቡቲ እና ኤርትራ እንዲሁም እንደ ዩጋንዳ ያሉ አገራት ለአገራችን ሰላም፣ ዲሞክራሲና ዘላቂ ልማት መረጋገጥ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳላቸው የማይካድ እውነታ ነው፡፡ አገራችን ከሌሎች አገሮች ጋር ስለሚኖራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ስናነሳ ጎረቤት አገሮችን በቀዳሚነት ማንሳት እንዳለብን በውጭ ጉዳይና አገራዊ ደህንነት ፖሊሲና ስትራቴጂ በግልፅ የተቀመጠ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህም፡ - 1. ኢትዮጵያ ከነዚህ አገራት ጋር ተመሳሳይ ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክና የተፈጥሮ ሀብት የሚጋሩ ህዝቦች ያሏት መሆኑ አገራቱ ከሌሎች አካባቢዎች በተለየ ከአገራችን ጋር ቀጥተኛ የሆነ ትስስር እንዲኖራቸው አድርጓል፡፡ 2. በእነዚህ አገሮች የሚኖር ሰላም እና ፀጥታ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ በአገራችን ላይ ቀጥተኛ ተፅእኖ አለው፡፡ ከዚህም በመነሳት አገራችን ከጎረቤት አገራት ጋር ባላት ግንኙነት ዙሪያ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራበት ነው፡፡ በአንድ በኩል ከብዙዎቹ ጋር ስትራቴጂክ አጋርነት መፈራረም ተችሏል፡ በሌላ በኩል ሰላም እና መረጋጋት የራቃቸው ጎረቤቶቻችንን ለማረጋጋት ህይወትም