ልጥፎች

ከዲሴምበር, 2016 ልጥፎች በማሳየት ላይ

Qabsoo farra malaammaltummaa obbo Duubee Jiloo

ምስል
  Qabsoon farra malaammaltummaa obbo dubee jiloo bu'aa argamsiisaa jira. Obbo Duubee Jiloo kanaan dura waggoota hedduuf Federeeshinii Atileetiksii Itiyoophiyaa keessatti itti gaafatamaa kutaa teeknikaa ta'uudhaan tajaajlaa turaniiru.Federeeshinicha keessatti turtii taasisaniin guddina Atileetiksii biyya keenyaatiif shoora gamasaanii akka gumaachan ni beekama. Obbo Duubee Jiloo rakkoo malaammaltummaa wajjin walqabatee dhiibbaa isaan irra gahaa tureen iddoo itti gaafatamaa qaban irraa ka'uuf dirqaman.Xalayaa barreessaniis hojiisaanii dhiisuuf gaafatan.Malaammaltoonni qaawwa kana barbaadan ammoo ariifannaa isaanii kanatti fayyadamuudhaan obbo Duubee Jiloo fedhiisaatiin itti gaafatamasaa gadi lakkiseera jedhanii himuuf jarjaran.Obbo Duubeen gochoota badiifi hojmaata badaa Federeeshinicha keessatti bu'ura gadi fageeffatee tures sab-quunnamtiilee gara garaa irratti dhiyaachuun saaxilaa turan. Wayita ammaa qabsoon farra malaammaltummaa obbo Duubee Jiloo taasisaa tur

ኢሕአዴግ ደምቆ ለመታየት የቀደሙ መንግስታትን አቧራ ማልበስ አያሻውም!

ምስል
በግል ከሌሎች ሰዎች ጋር በማደርገው ውይይትና በአንዳንድ አጋጣሚዎች በተሳተፍኩባቸው የውይይት መድረኮች ላይ ኢሕአዴግ ለምን ራሱን ካለፉት ስርዓቶች ጋር ያነፃፅራል? የሚል ጥያቄ ሲነሳ እሰማለሁ፡፡ የጥያቄው መነሻ የተለያየ ገፅታ ያለው የመሆኑን ያክል የጠያቂዎቹም ፍላጎት (motive) የተለያየ ሆኖ ይታየኛል፡፡ በእነዚህ ገፅታዎች ላይ ወደኋላ የምመለስበት ሆኖ አሁን አንዳንድ መሰረታዊ ጉዳዮችን ላንሳ፡፡ ዓለማችን በብዙ ልዩነቶችና አንፃራዊነቶች የተሞላች ነች፡፡ ስለሰለጠኑ አገራት በተለይም ስለ ሃብት መጠናቸውና ስለ ቴክኖሎጂ ምጥቀታቸው ለማውራት የእኛን ሀገር አይነት ታዳጊዎችን ማንሳት ያስፈልጋል፡፡ ስለ ኋላቀርነት ሳታውቅ የእሱ ተቃራኒ የሆነውን ስልጣኔ ልታደነቅ አይቻልህምና፡፡ ስለስንፍና ለማውራት ጉብዝናን መረዳት ግድ ይላል፡፡ ስለ መልካምነት ለማውራትም እንዲሁ የመጥፎነትን ገፅታ መለየት ግድ ይላል፡፡   እናም ንፅፅር ተፈጥሯዊ ነው፡፡ ይህ ሁኔታ የሚያሳየን ግን ንፅፅር ተፈጥሯዊ መሆኑን ብቻ ሳይሆን የተሻለ ግንዛቤ ለመፍጠርም ተፈላጊ ጉዳይ እንደሆነ ነው፡፡ አሁንም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ከ23 በመቶ የማያንሰው ከድህነት ወለል በታች መሆኑን እንድንረዳ፤ ከውስጣችን እንዲያመንና እንዲቆጨን በማሌዥያና ታይዋን ከድህነት ወለል በታች የሚኖረው ሕዝብ 5 በመቶ እንኳን እንደማይሞላ ማወቅ አለብን፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን የደርግ ስርዓት ሲወድቅ ከ50 በመቶ በላይ የሚሆነው የሀገራችን ሕዝብ ከድህነት በታች ይኖር እንደነበር ማወቃችን እስካሁን ድህነትን ለመቀነስ የተከተልነውን መንገድ የስኬታማነት መጠን ያስገነዝበናል፡፡ ስለዚህ ንፅፅራችን ከመነሻችንም ከመድረሻችንም መሆን አለበት፡፡ በሌላ በኩል ያለፈውን ማወቅ የወደፊቱን ለመተለም አይነተኛ መሳሪያም ነው፡፡ ካለፉ

የአዲስ አበባ አስተዳደር መጠነ ሰፊ መዋቅራዊ ለውጥ ሊያደርግ ነው

ምስል
- አምስት ምክትል ከንቲባዎች   ይኖራሉ - የመሬት ልማት ኮርፖሬሽን ይቋቋማል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተንሰራፋውን የመልካም አስተዳደር ችግርና እየበረታ ለመጣው የሕዝብ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት፣ በከተማው ታሪክ ከ14 ዓመታት በኋላ ትልቅ የተባለ የመዋቅር ለውጥ ሊያደርግ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር በከተማው መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል ጥናት እንዲያካሄድ ያቋቋመው፣ የአደረጃጀትና የመዋቅር ለውጥ ጥናት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ጥናቱን አጠናቋል፡፡ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ   ለከፍተኛ ባለሥልጣናትና ለመስኩ ባለሙያዎች ለውይይት የቀረበው ይኼ ጥናት፣ በፖለቲከኞችና በባለሙያዎች የሚያዙ ዘርፎችን ለይቶ አስቀምጧል፡፡ በጥናቱ መሠረት በፖለቲከኞች የሚመሩት ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ሲሆኑ፣ ሥራዎቹም ክትትልና ግምገማ ናቸው፡፡ በባለሙያዎች የሚመሩት ደግሞ ማዘጋጃ ቤታዊ ሥራዎች ናቸው፡፡ በዚህ መሠረት ከተማው አንድ ከንቲባና አምስት ምክትል ከንቲባዎች የሚኖሩት ሲሆን፣ ምክትል ከንቲባዎቹ የኢኮኖሚ ዘርፍ፣ የመሬት፣ የቤቶች ልማትና ኮንስትራክሽን ዘርፍ፣ የትራንስፖርት መሠረተ ልማትና አካባቢ ጥበቃ ዘርፍ፣ የማኅበራዊ ዘርፍ፣ የመልካም አስተዳደር፣ የፍትሕና የደኅንነት ዘርፍ ናቸው፡፡ ከንቲባውና አምስቱ ምክትል ከንቲባዎች ብቻ የከተማው ካቢኔ አባል ይሆናሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ 22 የካቢኔ አባል ቢሮዎች አሉት፡፡ በአዲሱ አደረጃጀት ቢሮዎቹ ከካቢኔ አባልነት ውጪ ተደርገዋል፡፡ በአዲሱ አደረጃጀት ቢሮዎች፣ ኤጀንሲዎች፣ የባለሥልጣን መሥሪያ ቤቶች፣ ጽሕፈት ቤቶችና በሥራቸው ያሉ ተቋማት የከተማ አገልግሎት ደረጃ ማውጣት፣ ተፈጻሚነታቸውን መከታተል፣ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን ማከናወን፣ ክትትልና ቁጥጥር ማ

Dogongora irraa of deebisuun ofumaaf tola!

ምስል
Leenjiin,haaromsaafi hawaasatti makamuun jijjiiramaaf haata’u! dhaamsa lammiiwwan keenya dhaqqabuu qabudha.Lammiiwwan kuma 9fi 855 jiddu galeessawwan adda addaatti leenjii haaromsaa hordofaa turan kaleessa irraa eegalee gadi lakkifamuudhaan gara maatii isaaniitti deebi’aniiru.Lubbuudhaan baraaramtanii baga carraa gara maatii keessanitti deebi’uu argattan! Kan carraa kana dhaban baay’eedha.Akka himamaa turettis Namoonni lakkoofsaan kuma 2 caalan gocha badii raawwataniin seeraan itti gaafatamuun isaanii dirqama waan ta’eef too’annoo jalatti hafaniiru.Kanaaf lammiiwwan amma gadi lakkifaman ni carrooman jechuun ni danda’ama.Umuriin ittiin turtan dhuunfaa keessan,maatiifi biyya keessaniif bu’aa gaarii kan ittiin galmeessiftan haata’u jedhamuun eebbifamuu qabu. Jeeqamsi biyya keenya naannolee adda addaatti mudate waan adda addaa nutti mul’isuudhaan darbeera.Mootummaan amma jiru kun jeeqamsaan taayitaa isaarraa bu’uu danda’a jechuun kan abdataniifi olola sobaa humnoota badii biyya alaa

Bu’ura maxxantummaa diiguuf hojjetamuu qaba!

Maxxantummaan hiika addaa hinqabu.Maxxantummaan Ilaalcha of tuulmmaafi dhiphimmaati.Maxxantummaan ilaalchaafi gochaan balaa ol’aanaadha,Nama balleessa,biyya miidha.Utuu maxxantummaan jiraachuu baatee hunduu waqixa deema.Sababa maxxantummaatiin imala walqixxummaatti gufuun uumame. Barreeffama kanaan abbaa dhiphummaafi of tuulummaa kan ta’e maxxantummaa kaaseen sukkuumee ilaaluu barbaade.Nuti akka sabaatti sababa maxxantummaatiin waan dhabneefi arganne ilaaluun barbaade.dubbisa gaarii isiniif haata’u. Maxxantummaan gufuu walqixxummaafi waldanda’uuti.Rakkoo kana mala kamittuu fayyadamuudhaan dhabamsiisuun barbaachisaadha.Maxxantummaan dhabamu malee walqixa fayyadamuufi jiraachuun rakkisaa ta’a.Kanaaf hundumtuu maxxantummaa irratti kutannoodhaan qabsaa’uudhaan akka dhabamu taasisuun dirqama ta’uu qaba. Bu’urri maxxanxummaa maalinni? jechuun gaafachuun murteessaadha.Dhiphummaafi of-tuulummaan bu’ura of danda’e qabu.Bu’urri ilaalchaafi gocha dhiphummaa gadaantummaadha.Kan gadi qabee

Dirqama hooggansa keenya haarawa irraa eegamu

Sadarkaa Federaalaattis ta’e Naannoleetiin rakkoolee kanaan dura ummanni bal’aan ittiin dararame qorannoon adda baasuudhaan kan hanqina qabu iddoo irraa akka ka’u taasisuun iddoowwan itti gaafatamaa baay’ee irratti hooggansi haarawaan ramadameera,muudameera.Tarkaanfiiwwan kutannoo Dh.D.U.O/A.D.W.U.I’tiin fudhataman kun galma yaadame bira ga’uu kan danda’an hooggansi haarawaan sadarkaa sadarkaan jiru adeemsa barame qofa utuu hintaane tooftaa hooggansaa ofiif horatetti fayyadamuudhaan iddoo itti ramadametti hooggansa sirriifi cimina qabu kennuu yoo danda’e qofadha. Kana gochuuf ammoo hooggansi haarawaan hunda dura ummata tajaajilamu amansiisuudhaan of maddii hiriirsuun dirqama isaati.Haala qabatmaa wayita ammaatti sadarkaa biyyaatiinis ta’e naannoleetiin jiruun dhiibbaadhaan utuu hin taane dhimma kamirrattuu ummata bal’aa hirmaachisuudhaaniifi abbaa taasisuudhaan socho’uun dirqama yoomiyyuu bira hindarbamne ta’eera.Dhimmaa kamirrattuu ummata bal’aa amansiisuudhaan ala eessumayyuu ga’

ለራስ ብቻ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠር ወጥተን ኢትዮጵያን እንመልከት

ምስል
አንዳንድ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና የፖለቲካ ተንታኝ ነኝ ባይ ሰዎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች   አብዮታዊ ዴኖክራሲያዊ ግንባር(ኢህአዴግ) በማካሄድ ላይ ያለውን ጥልቅ ተሃድሶ ለማጣጣልና ዋጋ ለማሳጣት ሲፍጨረጨሩ ይታያል፤እነዚህ ሰዎች በአንድ ወቅት በሰነቁት መልካም ተስፋ ወደ ፖለቲካው መንድር የገቡና ኢህአዴግን በምርጫ ለማሸነፍ ጥረት ያደረጉ፤ነገር ግን በውድድር ሂደት በደረሰባቸው ሽንፈት ጥጋቸውን ለመያዝ የተገደዱ የከሰሩ ፖለቲካኞች ናቸው።አቶ ገብሩ አስራትና አቶ ሙሼ ሰሙ፣ሁለቱ ሰዎች ሰሞኑን አዲስ አድማስ በተባለ የግል ጋዜጣ ላይ የወቅቱን ሁኔታ አስመልከተው የሰጡትን ቃለ መጠይቅ ለማንበብ እድሉን አገኘሁና የሁለቱንም ሰዎች ሃሳብና አመለካከት በትኩረት ማየት ተገቢ እንደሆነ አሰብኩ አቶ ገብሩ አስራት በአንድ ወቅት በኢህአዴግ ፖሊሲዎች ላይ ተመስርተው የትግራይን ክልል የመሩና በ1993 ክፍፍል ወቅት በተፈጠረው አንጃ ውስጥ ተቀላቅለው በተሸናፊው አንጃ ውስጥ ተካትተው ከተለዩ በኋላ አረና የተባለ ተቃዋሚ ፓርቲ የመሰረቱና እስከ አሁን ምንም ውጤት ማስመዝገብ ያልቻሉ ሰው ናቸው አሁን የፖለቲካ ተንታኝ የተባሉት አቶ ሙሼ ሰሙ ደግሞ በአንድ ወቅት የአዴፓ ከፍተኛ አመራር የነበሩና በራሳቸው ፈቃድ ከፓርቲው መልቀቃቸውን ይፋ አድርገው የነበሩ ናቸው በዚህ ፅሁፌ በስም የጠቀሱኩዋቸውን ሰዎች ጨምሮ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር የሚገኙ የከሰሩ ፖለቲካኞች በጥልቅ ተሃድሶ ሂደት ላይ በማካሄድ ላይ ያሉትን ዘመቻ በቅደም ተከተል ለማጋለጥ እሞክራለሁ “ኢህአዴግ በዚህች ሃገር ተቃዋሚ እንዳይኖር እያደረገ ነው፡፡ከራሱ የተለየ ሃሳብ፣ አቋምና አቅጣጫ ያለው ግለሰብ እንዲኖር አይፈልግም፡፡ጠላት ብሎ ነው የሚፈርጀው።ተቃዋሚዎች በዚህ አመለካከት ብዙ በደል ነው የደረ

ዳግማዊ ጥልቅ ተሃድሶው የእነ ቶሎ ቶሎ ቤት…. እንዳይሆን

ምስል
የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ጥልቅ ተሃድሶ በመካሄድ ላይ እንዳለ ይታወቃል።ተሃድሶ ሂደት እንደሆነና በአንድ ወቅት የማይጠናቀቅ መሆኑ ሲነገርም ይሰማል፤እውነት ነው ተሃድሶ በሂደት ከግቡ መድረስ የሚችል መሆኑ ላይ ሁሉም ወገን መግባባት መቻል አለበት ነገሩ የእነ ቶሎ ቶሎ ቤት ግድግዳው ሰንበሌጥ አይነት መሆን የለበትም የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች በማካሄድ ላይ የሚገኙትን ጥልቅ ተሃድሶ ላይ ተመስርተው የአመራር ለውጥ በማድረግ አዳዲሶቹን አመራሮች ለተገልጋዩ ሕዝብ አስተዋውቀው ይፋ አድርገዋል መልካም ነው ነገር ግን በግንባሩ አባል ድርጅቶች ውስጥ እስከ አሁን በየደረጃው የተደረገው የአመራር ለውጥ ከፍና ዝቅ ያለበት ሁኔታ ታይቶበታል፤በዚህ ረገድ የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት(ኦህዴድ) የወሰደው እርምጃና በየደረጃው ያካሄደው የአመራር ለውጥ የተሻለ እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ ስለዚህ ቀደም ሲል የተካሄደው የሌሎች እህት ድርጅቶች የተሃድሶ እንቅስቃሴና በአመራሮች ላይ የተወሰደው እርምጃ ለምን ከኦህዴድ ያነሰ ሆኖ ተገኘ?ብለው የሚጠይቁ ወገኖች አሉ የጥያቄው መነሻ የኦህዴድ ሊቀመንበር አቶ ሙክታር ከድር እና ምክትል ሊቀመንበሯ ወይዘሮ አስቴር ማሞ ሙሉ በሙሉ ከሃላፊነታው መነሳታቸው ነው፤ከዚህም ሌላ በኦሮሚያ ክልል በተለያየ ደረጃ በአመራር ላይ የነበሩ በርካታ ሰዎች በአዲስ ተተክተዋል፤ቀሪዎቹም ከነበሩበት የሃላፊነት ቦታ ወደ ሌላ እንዲዛወሩ ተደርጓል ይህም መልካም ነው ነገር ግን በዋናነት የስርአቱ አደጋዎች ናቸው ተብለው የተለዩት ችግሮች  የጥበትና ትምክህት(ጥገኝነት) አመለካከቶችና ድርጊቶች፤ኪራይ ሰብሳቢነት፤አክራሪነት፤ስልጣንን ለግል ኑሮ ማደላደያ አድርጎ መጠቀም በሕወሃት፤በብአዴንና በደኢህዴን ሰዎች ውስጥ የነበረው የስርአቱ አደጋ በጥቂቱ ነው ያ

ሃና ጎሜዝና ኢትዮጵያ

ምስል
ወይዘሮ አና ጎሜዝ የ1997 ምርጫ ሂደትን በኢትዮጵያ ተገኝቶ የታዘበው የአውሮፓ ታዛቢ ቡድን መሪ ሆና ሰርታለች የወቅቱን ምርጫ ሂደት በተመለከተም የምርጫው አሸናፊ ተቃዋሚዎች ናቸው በሚል ሪፖርት ብታቀርብም ሪፖርቷን የአውሮፓ ህብረት አጣጥሎ ውድቅ አድርጎባታል ወይዘሮዋ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በያዘችው ቂም እኝኝ እያለች ይኸው እስከ አሁን ጥርሷን እንደነከሰችብን አለች፤እረ ወይዘሮ ሃና እባክሽ ተይን እኛ ኢትዮጵያዊያን የሰው አንፈልግም የራሳችንንም አንሰጥም። ነገርን ነገር ያነሳዋል አለ ያገሬ ሰው፤ የወቅቱ ምርጫ ውጤት ይፋ ከተደረገ በኋላ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ መለስ ዜናዊ ሴትዮዋን የተመለከተ አንድ ረዥም ፅሁፍ በኢንግሊዝኛ ቋንቋ አሳትመው ማውጣታቸውን አስታውሳለሁ፤ፅሁፉ የወይዘሮ አና ጎሜዝን መሰሪ አካሄድ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ በመሆኑ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሴትዮዋ ብርቱ የኢትዮጵያ ጠላት ሆና  ቁጭ አለች። አሁን ባለው ሁኔታም ባገኘችው አጋጣሚ ሁሉ ኢትዮጵያን የሚጎዳ ነገር ከመስራት አርፋ እንደማትቀመጥ ተናግራለች መባሉን ሰምቼ ሳቄን ለቀቅሁት፤እውነት ከጣሪያ በላይ ነው የሳቅሁት።እና ይህቺ ሴት አዲሱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ዘመዴ ስለሆነ እንደምንም ብዬ ኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ እንዲጥል አደርጋለሁ አለች አሉ ወይ ሃና ጎሜዝ። ወይዘሮ ሃና የኢትዮጵያን ተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ወደ አውሮፓ ጠርታ የምትወሰውሰው አንሶ አሁን ደግሞ በተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ ባለስልጣን ልትመጣብን ነው ማለት ነው፤እረ ይህቺን ሴትዮ ምን እናድርጋት? እኛ ኢትዮጵያዊያን መቼም ቢሆን እጅ አንሰጥም ወይዘሮ አና ጎሜዝ ይህን የምታውቅ አይመስለኝም።ስለዚህ እዚያ ብራስልስ የምትገኙ የእኛ ሰዎች በ