ልጥፎች

ከኖቬምበር, 2017 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ በድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ላይ የእርምት እርምጃ ወሰደ

ምስል
የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ /ህወሓት/ ማዕከላዊ ኮሚቴ በድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ። በዚህ መሰረት የድርጅቱ ሊቀ መንበር አቶ አባይ ወልዱ ከድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው ተነስተው በድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ዝቅ ብለው እንዲያገለግሉ ወስኗል።   በተጨማሪም የድርጅቱ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ በየነ ምክሩም ወደ ድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ዝቅ ብለው እንዲሰሩ መወሰኑን ድርጅቱ ለጣቢያችን በላከው መግለጫ አስታውቋል።   ከዚህ ባለፈም የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ወይዘሮ አዜብ መስፍንን ከስራ አስፈጻሚ አባልነታቸው እና ማዕከላዊ ኮሚቴው ታግደው እንዲቆዩ መወሰኑንም ገልጿል።   ድርጅቱ ከዚህ በተጨማሪም ለሌሎች ሁለት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።   እርምጃው ማዕከላዊ ኮሚቴው ያካሄደውን ጥልቅ ግምገማ ተከትሎ የተወሰደ ነው።   ማዕከላዊ ኮሚቴው ባለፈው ሳምነት ባወጣው መግለጫ በአመራር ስትራቴጂካዊ ፖለቲካዊ ሁነቶች፣ ሁለንተናዊ የልማታዊ ትራንስፎርሜሽን ማረጋገጥ እና በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዙሪያ በጥልቅ በመገምገም ያሉትን መሰረታዊ ክፍተቶች በዝርዝር ማየቱን ገልፆ ነበር።   በትግልና በመርህ የተመሰረተ አንድነት አለመኖር፣ በመጠቃቃትና መከላከል ዝምድና ላይ መመስረት፣ የፀረ ዴሞክራሲ ጥልቅ አስተሳሰብና ተግባራት መኖራቸውን መገምገሙንም በመግለጫው ማስታወቁ ይታወሳል።   በተጨማሪም የወጣቱን ትውልድ እና የምሁሩን አቅም በመገንባት፣ በማሰለፍና ተጠቃሚ በማድረግ ረገድ መሰረታዊ ጉድለቶች መኖራቸውን ገምግሞ ነበር።   በክልሉም  ትራንስፎርሜሽን ከማረጋገጥ አኳያ መሰረታዊ ስትራቴጂካዊ የአመራር

በኢዴፓ አመራሮች መካከል አለመግባባት ተፈጥሯል

ምስል
በኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) አመራሮች መካከል አለመግባባት ተፈጥሯል። ሁለት የፓርቲው ነባር አመራሮች በየራሳቸው ወገን የፓርቲ ፕሬዚዳንት መሆናቸውን ገልጸዋል። የፓርቲው ዋና ጸሃፊ አቶ ሳህሉ ባዬ የቀድሞው የድርጅቱ ሊቀ መንበር በመርህ ጥሰት ምክንያት ከስራ መነሳታቸውን ለፋና ብሮድካስቲን ኮርፖሬት ተናግረዋል። ፓርቲው ለበርካታ ዓመታት በሊቀ መንበርነት የመሩት ዶክተር ጫኔ ከበደን በመርህ ጥሰት ምክንያት ከሀላፊነት መነሳታቸውን የፓርቲው ዋና ጸሃፊ አቶ ሳህሉ ባዬ ገልፀዋል። ዶክተር ጫኔ ከበደ በበኩላቸው “የፓርቲው ሊቀ መንበር እኔ ነኝ፤ እኔን ያወረደ ስራ አስፈፃሚም ሆነ ጠቅላላ ጉባኤም የተካሄደ የለም” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። የፓርቲው ብሄራዊ ምክር ቤት ባደረገው ስብሰባ ዶክተር ጫኔ ከበደን በማንሳት፥ አቶ አዳነ ታደሰን መሾሙንም ነው አቶ ሳህሉ ባዬ ሲሉ ተናግረዋል። ከስልጣን ተነስተዋል የተባሉት ዶክተር ጫኔ ከበደ በበኩላቸው፥ እርሳቸው የሚመሩት የኢዴፓ ፓርቲ አሁንም እንዳለ ገልጸዋል። የተደረገው ነገርም ህገ ወጥ ነው አሁንም የፓርቲው ሊቀ መንበር እኔ ነኝም ብለዋል። እርሳቸው አቶ ሳህሉ ዋና ጸሃፊነታቸውን ተጠቅመው ህገ ወጥ ድርጊት ፈጽመዋል ያሉ ሲሆን፥ ጉዳዩ በፍርድ እየታየ መሆኑን ነው የጠቀሱት። በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሰረት ብሄራዊ ምክር ቤቱ ከጠቅላላ ጉባኤው የፓርቲውን ስራ አስፈፃሚ የመሾም እና የመሻር ስልጣን ተሰጥቶታል። ይህን ስልጣኑን ተጠቅሞም ከምክር ቤቱ አባላት መካከል 18 አባላት በተገኙበት ጉባኤ በማካሄድ፥ ዶክተር ጫኔ ከበደ ከስልጣናቸው መነሳታቸውን አቶ ሳህሉ ባዬ ገልፀዋል። ከጠቅላላ ስራ አስፈፃሚ መካከል ሶስቱ ከሃላፊነታቸው ተነስተው ወደ ብሄራዊ ምክር

በሕግ የበላይነት ሥር የማይተዳደር አገር የሕገወጦች መጫወቻ ይሆናል!

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ በአንክሮ የሚከታተል ማንኛውም ሰው በርካታ ግራ የሚያጋቡና አወዛጋቢ ጉዳዮች ይገጥሙታል፡፡ ዋና ዋና በሚባሉት ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መስኮች ውስጥ በየዕለቱ የሚያጋጥሙ አደናጋሪ ጉዳዮች ላይ በግልጽ መነጋገርና የጋራ መግባባት መፍጠር ካልተቻለ የአገሪቱም ሆነ የሕዝቡ ዕጣ ፈንታ ያሳስባል፡፡ በአንድ አገር ሰላምና መረጋጋት የሚኖረው ሕዝብ በነፃነት መኖሩ ሲረጋገጥ ነው፡፡ ይህ ነፃነት የሚገኘው ደግሞ በሕግ የበላይነት ሥር መኖር ሲቻል ነው፡፡ የሕግ የበላይነት መንግሥት በነፃና ፍትሐዊ ምርጫ ብቻ እንዲመሠረት፣ የፀጥታ ኃይሎች ለማንም ወገንተኛ ሳይሆኑ ሕግ ብቻ እንዲያስከብሩ፣ የመንግሥት ተሿሚዎች ሥልጣናቸው በሕግ የተገደበ እንዲሆን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሕጋዊና ሰላማዊ ሆነው ዓላማቸውን እንዲያስፈጽሙ፣ የአገሪቱ ዜጎች በሕግ ፊት እኩል መሆናቸው እንዲረጋገጥ፣ መደራጀትና ሐሳብን በነፃነት መግለጽ ባህል እንዲሆን፣ ራሳቸውን ከሕግ በላይ ለማድረግ የሚፈልጉ ጉልበተኞች በሕግ እንዲዳኙ፣ ወዘተ. ትልቅ አስተዋጽኦ አለው፡፡ የሕግ የበላይነት ሲጣስ ግን ሥርዓት አልበኝነት ይነግሣል፡፡ የዜጎች ደኅንነት ለአደጋ ይጋለጣል፡፡ አምባገነንነት ይንሰራፋል፡፡ ይህ ደግሞ ለ21ኛው ክፍለ ዘመን አይመጥንም፡፡ የሕግ የበላይነትን የማይቀበል በሰላም መኖር አይችልም፡፡ ሕግ የማያከብርና የማያስከብር መንግሥት ራሱን ለአደጋ ከማጋለጡም በላይ አገርንና ሕዝብን ትርምስ ውስጥ ይከታል፡፡ ዜጎች የሚያዳምጣቸው ካጡ ሕግ እንዳልተከበረ መተማመን ያስፈልጋል፡፡ የመልካም አስተዳደር ዕጦትና የፍሕት መጥፋት የሕግ አለመከበር ውጤት ነው፡፡ ሙስና ተንሰራፍቶ አገር እየተዘረፈች ከሆነ የሕግ የበላይነት ሳይሆን ሕገወጥነት ተስፋፍቷል ማለት ነው፡፡ የፈለገ

Kokkee walqabuu!

Humni farra kiraa sassaabdotaafi kiraa sassaabdoonni bara taayitaa isaaniitti waa fuffnannatan kokkee wal qabuudhaan qabsoo cimaarra jiru. Kiraa sassabdoonni lubbuu dheereeffachuuf wixiffachaa akka jiranis qabatamaan argaa jirra.Kutannoon humna farra kiraa sassaabdotaas sadarkaa hammamiitiin abdachiisaa akka ta'e qabatamaan mul'achaa jira. Kiraa sassaabaan qabsoo irratti eegalame karaa irraa dabsuuf humna walitti kuufate qaba.Keessumattuu maallaqa seeraan ala walitti qabateen tarkaanfii irratti fudhatamu ofirraa ittisuuf wanti inni hin goone hin jiru. Egaa akkuma hubatamaa jiru qabsoon ammaan boodaa daran hadhaawaadha.Qabsoon hadhaawaan kun bu'aa mi'aawaa barbaadamu akka argamsiisuuf ummata bal'aadhaan kan deeggarame ta'uu qaba! Ummanni keenya kutannoo hooggansa haaromsaa hubateera.Waan gochuu qabu irrattis akka waliigale haaluma qabatamaan jirutu mul'isa.Bassoofi aannantu wal arge jechuun ni danda'ama. Kana jidduutti kanneen

‹‹በእኔ ዕይታ የአፈጻጸም ክፍተት ካልሆነ በስተቀር የፌዴራል ሥርዓቱ ችግር አላመጣም››

ምስል
‹‹በእኔ ዕይታ የአፈጻጸም ክፍተት ካልሆነ በስተቀር የፌዴራል ሥርዓቱ ችግር አላመጣም›› ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የኢፌዴሪ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ከ1987 ዓ.ም. እስከ 1993 ዓ.ም. የኢፌዴሪ ርዕሰ ብሔር ወይም ፕሬዚዳንት ነበሩ፡፡ ከዚያ በፊት በሽግግሩ ጊዜ በመጀመርያ የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር፣ በኋላ የማስታወቂያ ሚኒስትር፣ እንዲሁም ጎን ለጎን የፓርላማ አባል ነበሩ፡፡ ከ1984 ዓ.ም. እስከ 1987 ዓ.ም. ሥራ ላይ የነበረውና የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥትን ያረቀቀው የሕገ መንግሥት አርቃቂ ኮሚሽንም አባል ነበሩ፡፡ ሕገ መንግሥቱን ያፀደቀው የሕገ መንግሥት ጉባዔም አባልና ሰብሳቢ ነበሩ፡፡ በሐምሌ ወር 1983 ዓ.ም. የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦሕዴድ)ን የተቀላቀሉት ለረዥም ዓመታት ይኖሩበት ከነበረው ጀርመን በመምጣት ነበር፡፡ ኦሕዴድን በመወከል ለአሥር ዓመታት በተለያዩ ኃላፊነቶች ሲሠሩ ከቆዩ በኋላ በ1993 ዓ.ም. በፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ምክንያት ከኦሕዴድም ሆነ ከኢሕአዴግ ተለይተዋል፡፡ ከ1998 ዓ.ም. እስከ 2002 ዓ.ም. በግል ተወዳድረው በማሸነፍ የፓርላማ አባል ነበሩ፡፡ የተቃውሞውን ፖለቲካ ከተቀላቀሉ በኋላ ደግሞ የአንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ (አንድነት) ሊቀመንበርና የውጭ ግንኙነት ኃላፊም ነበሩ፡፡ መድረክ እንዲቋቋም ተነሳሽነት ከወሰዱ ግለሰቦችም አንዱ ናቸው፡፡ ሰለሞን ጎሹ የሕገ መንግሥቱን ዲዛይንና አፈጻጸም በተመለከተ የሚነሱ ውዝግቦችንና የኦሕዴድ አዲስ አመራሮችን የአመራር ዘይቤ ጨምሮ በተለያዩ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ አነጋግሯቸዋል፡፡ ሪፖርተር ፡- በምርጫ 2007 በፌዴራልም ሆነ በክልል ደረጃ ያሉ ምክር ቤቶችን ሙሉ በሙሉ እንዳሸነፈ በምርጫ ቦርድ የተነገረለት

በስም ማጥፋት ተግባር ውስጥም ሆነ በሌሎች አላስፈላጊ ጉዳዮች እየተሳተፉ የሚገኙ ዕድሜያቸውን ለማሳጠር እየጣሩ ያሉ አካላት ናቸው››

ምስል
‹‹በስም ማጥፋት ተግባር ውስጥም ሆነ በሌሎች አላስፈላጊ ጉዳዮች እየተሳተፉ የሚገኙ ዕድሜያቸውን ለማሳጠር እየጣሩ ያሉ አካላት ናቸው›› ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)፣ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤትና በሚኒስትሩ ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ የከፈቱ ባለሥልጣናትም ሆኑ ግለሰቦች፣ ዕድሜያቸውን ማሳጠር የፈለጉ ናቸው ሲሉ ሚኒስትሩ ነገሪ ሌንጮ ( ዶ / ር ) ተናገሩ። ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት ሰኞ ኅዳር 11 ቀን 2010 ዓ.ም. የበጀት ዓመቱን የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸምና ቀጣይ ዕቅድ ለምክር ቤቱ የባህል፣ ቱሪዝምና መገናኛ ብዙኃን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሲያቀርቡ ነው። ሚኒስትሩ ስለገጠማቸው የስም ማጥፋት ዘመቻ ለቋሚ ኮሚቴው ባቀረቡት ሪፖርት ውስጥ ያካተቱት ነገር ባይኖርም፣ የኮሚቴው አባላት ግን በጽሕፈት ቤቱና በሚኒስትሩ ላይ እየተፈጸመ ነው ስላሉት የስም ማጥፋት ዘመቻ በጥያቄ መልክ አቅረበውላቸዋል። የቋሚ ኮሚቴውና የፓርላማው አባል አቶ ወንድወሰን መኮንን በኢሕአዴግና በኢሕአዴግ ድርጅቶች ጥላ ሥር ሆነው ጎጠኝነትና ዘረኝነትን የሚያስፋፉ፣ በጽሕፈት ቤቱና በሚኒስትሩ ላይም የስም ማጥፋት ዘመቻ እየፈጸሙ መሆኑን ተናግረዋል። ‹‹ እንደ አገር እናስብ ካልን የሚጠቅመን ኢትዮጵያዊነታችን እንጂ ዘረኝነትና ጎጠኝነት አይደለም፤ ›› ያሉት የምክር ቤቱ አባል፣ ‹‹ ኢሕአዴግን ተጠልለው እንዴት ነው ዘረኝነትን በኦፊሴላዊ ደረጃ የሚያራምዱት? ›› ሲሉ ጠይቀዋል። ጽሕፈት ቤቱን ያቋቋመውም ሆነ ሚኒስትሩን

Qabsoon Oromoo Finfinnee keessattis finiinaa jira!

ምስል
Konfaransiin dhaabbattummaa Dh.D.U.O 7ffaan Magaalaa Finfinneetti tibbana hooggantoota miseensota dhaabbatichaa kutaalee magaalichaa kurnan keessatti guyyoota lamaaf haala ho’aa ta’een erga geggeeffameen booda, guyyaa 3ffaasaatti ammoo iddoo tokkotti Galma Aadaa Oromoo Finfinneetti milkaa’inaan xumuramee jira. Konfaranicha irratti qabxiileen mariif ka’umsa ta’an dhihaatanii gadi fageenyaan irratti mari’atameera.   Gaaffiwwan jajjaboon dhimmoota mirgoota, fedhiifi faayidaa ummata Oromoo heera mootummaatiin taa’e eegsisuu fi kabachiisuu irratti fuulleeffatan ka’anii irratti mar’atamaniiru. Hojiirra Oolmaan sirna Federaalizimii biyyatti, gaaffii keessa galuu Ol’aantummaa heeraa fi seeraas qabxii xiyyeeffannaa hirmaattotaa ta’eera.   Kun qabsoo injifannoo Sabichaa as dhiheessuuf taasifamaa jiru, Finfinnee keessattis finiinaa jiraachuu agarsiisa. Kanaaf ammoo ka’umsa kan ta’e qabsoo ummanni Oromiyaa daangaa hanga daangaatti tokkummaan socha’ee geggeessaa jiruufi Mootummaasaaf ta’u a

ሼክ አል አሙዲ ታስረው እየተመረመሩ ነው

ምስል
የሚድሮክ ኢትዮጵያ ሊቀመንበር ሼክ መሐመድ አል አሙዲ በሳዑዲ ዓረቢያ በተጀመረው ፀረ ሙስና ዘመቻ ታስረው እየተመረመሩ ነው፡፡ የሳዑዲ ዓረቢያን ፀረ ሙስና ዘመቻ የሚመሩት የአገሪቱ አልጋ ወራሽ ልዑል መሐመድ ቢን ሳልማን ቅዳሜ ጥቅምት 25 ቀን 2010 ዓ.ም. አመሻሽ ላይ በታዋቂው ሪትዝ ካርልተን ሆቴል በቁጥጥር ሥር ካዋሏቸው 11 ልዑላንና 38 ታዋቂ ባለሀብቶች መካከል አንዱ የሆኑት ሼክ አል አሙዲ፣ በሙስና ተጠርጥረው እየተመረመሩ ይገኛሉ፡፡ የአገሪቱ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ሼክ ሳውድ አል ሞጀብ የፀረ ሙስና ዘመቻው በሳዑዲ ዓረቢያ የተንሰራፋውን ሙስና ለመንቀል ጅማሮ ነው ብለዋል፡፡ የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት በቁጥጥር ሥር ያዋላቸው ግለሰቦች ሀብቶችና ኢንቨስትመንቶች መታገዳቸው ታውቋል፡፡ በዚህ መሠረት የሼክ አል አሙዲ በሳዑዲ ዓረቢያ ያሏቸው ኢንቨስትመንቶች የታገዱ ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ ያላቸው ኢንቨስትመንቶች ላይ ዕገዳ አይኖርም ተብሏል፡፡ ለንደን የሚገኙት የሼኩ ቃል አቀባይ ከሳዑዲ ዓረቢያ ውጪ ያሉ የባለሀብቱ ኢንቨስትመንቶች ምንም እክል እንደማይገጥማቸው ለብሉምበርግ ተናግረዋል፡፡ በሳዑዲ ዓረቢያ እየተካሄደ ያለው የንጉሣዊ አገዛዙ የውስጥ ጉዳይ ነው ያሉት ቃል አቀባዩ ቲም ፒንድሪ፣ ሼኩ ከሳዑዲ ውጪ ያሏቸው ሀብቶችና ኢንቨስትመንቶች ችግር እንደማይገጥማቸው ገልጸዋል፡፡ ሼክ አል አሙዲ በኢትዮጵያ ውስጥ ባሏቸው ኢንቨስትመንቶች ለ50 ሺሕ ያህል ሰዎች የሥራ ዕድል የፈጠሩ ሲሆን፣ ይህም ከመንግሥት ቀጥሎ ትልቁ የሥራ ዕድል ፈጣሪ ባለሀብት አድርጓቸዋል፡፡ የእሳቸው በቁጥጥር ሥር መዋል ከተሰማ በኋላም ኢትዮጵያ ውስጥ መደናገርና መደናገጥ ተፈጥሯል፡፡ ሪፖርተር በዚህ ጉዳይ ላይ ያነጋገራቸው የሚድሮክ ኢትዮጵያ የሥራ ኃላፊዎችም ግራ መጋባታቸውን ከመግለጽ

በሕዝቦች ትስስርና አንድነት እንደሰት!

ምስል
የኦሮሞና አማራ ሕዝቦች ትስስርን ለማጠናከር በሁለቱ ክልሎች አመራሮች የአገር ሽማግሌዎች፤አባ ገዳዎች፤ምሁራንናና ታዋቂ ሰዎች የተሰራው ስራ እጅግ በጣም ውጤታማ ሆ ኗል ይህ አመርቂ ውጤት ብዙዎችን አስደስቶ ሲያስፈነድቅ ጥቂቶችን ግን አንገት አስደፍቶ በማስቆዘም ላይ ይገኛል፤በሰሞኑ የኦሮሞና የአማራ ሕዝቦች ትስስርና አንድነት ማጠናከሪያ መድረክ አነማን ተደሰቱ? እነማንስ ተከፉ? በዝርዝር እንየው…. በዚህ የህዝቦች ትስስር ደስተኛ የሆኑቱ በዴሞክራሲያዊ አንድነት የሚያምኑ ኃይሎች ናቸው፤የዴሞክራሲያዊ አንድነት ደጋፊዎችም የደስታው ተካፋዮች ናቸው በሕዝቦች ትስስርና አንድነት እነርሱም ተጠቃሚ ስለሆኑ መደሰታው ምክንያታዊ ነው የህዝቦችን ትስስር ለማጠናከር በማንኛውም አካል የሚከናወን ስራ ሊደገፍ እንጂ ሊኮነን አይገባም! እውነት ነው የኦሮሚያና የአማራ ክልል አመራሮች ድንቅ ስራ ነው ያከናወኑት በዚህ ሊመሰገኑ ይገባል የህዝቦችን ትስስርና አንድነት ለማጠናከር በሃቅ የሰሩ ወገኖች ሁሉ ምስጋና ይገባቸዋል፤ይህ የህዝቦች ትስስር ማጠናከሪያ ስራ ቀጣይነት ያለው መሆን አለበት  የኦሮሚያ ሕዝብ ወደፊት በተመሳሳይ ከትግራይ ከደቡብ ብሄር ቤሄረሰቦችና ከሌሎችም ክልሎች ሕዝቦች ጋር ያለውን ታሪካዊ ትስስር አጠናክሮ ይቀጥላል በዚህ የሚከፉ ጥቂት ወገኖች ቢኖሩም የህዝቦችን ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ የተለያዩ ስራዎች መከናወን አለባቸው በአመት አንድ ጊዜ ብቻ የሚመጣው የብሄር ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ክብረ በዓል ብቻ በቂ አይሆንም አይደለም፤ሕገ መንገስታችን የፀደቀበትን ወቅት ምክንያት በማድረግ ሕዳር 29 በየዓመቱ የሚከበረው የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ቀን እንዳለ ሆኖ በፈጠራ ስራ የታገዙ ሌሎች የሕዝባዊ ትስስሮሽ ማጠናከሪያ መድረኮች በየወቅቱ ሊኖ

የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት(ኦህዴድ) 7ኛ ደርጅታዊ ኮንፍራንስ ተሳታፊዎች የአቋም መግለጫ

ምስል
የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት(ኦህዴድ) 7ኛ ደርጅታዊ ኮንፍራንስ ተሳታፊዎች የአቋም መግለጫ የኦሮሞ ሕዝብ የዛሬው ዘመናዊ ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር ምንጭ ሆኖ የሚታየው የገዳ ስርዓት ባለቤትና በዚህም ራሱን ሲያስተዳድር የቆየ፤ይህንኑ ለአለም ያበረከተ ህዝብ ነው ይህ ስርዓት በባህሪው አንድነትን የሚያውጅና አብሮ መኖርን የሚያጠናክር ነው ዛሬም ቢሆን የኦሮሞ ሕዝብ በዘመናዊ አስተዳደር ውስጥ  የራሱን መንግስት መስርቶ እየተመራበት በስርዓታችን ውስጥ ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች  የልማት፤የሰላምና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እንዲሁም የኦሮሞን ሕዝብ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ የአመለካከት አንድነት በመፍጠር የድህነትን ዕድሜ ለማሳጠር ጠንከረን በመስራት ላይ እንገኛለን እኛ የኦህዴድ 7ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች ከጥቅምት 19 እስከ ጥቅምት 23 በአዳማ ገልማ አባ ገዳ ስናካሂድ የቆየነውን ኮንፍራንስ በተሳካ ሁኔታ አጠናቅቀናል የጥልቅ ተሃድሶ አካል በየሆነው በዚህ ድርጅታዊ ሰባተኛ ኮንፍራንስ ላይ በተሃድሶ ንቅናቄ ውስጥ ለሕዝባችን በገባነው ቃል መሰረት አፈፃፀሙን ገምግመን በቀጣዩ የትግል አቅጣጫ ላይ መግባባት ላይ ደርሰናል የፖለቲካ፤የኢኮኖሚና የዴሞክራሲ ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ምላሽ ማግኘት እንዳለባቸው ተስማምተናል የፌዴራል ስርዓታችንን በማጠናከር ስራ ወስጥ ሕዝብና አመራሩ ሚናውን መወጣት ያለበት መሆኑ ወሳኝ እንደሆነ፤በሕገ መንግስቱ ላይ የተረጋገጡ መብቶች ሳይሸራረፉ ተግባራዊ እንዲሆኑ የድርጅቱ አባላትና አመራሮች ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸው፤በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል በተፈጠረው ብጥብጥ በሰው ሕይወት በአካልና በንብረት ላይ በደረሰው ጉዳት ከፍተኛ ሃዘን የተሰማን ሲሆን የዚህ ችግር ምንጭ የሕዝባችን ፍላጎት እንዳልሆነ ተረድተናል የተከሰተው ች

Murteewwan gurguddoo koonfaransii dhaabbatummaa 7ffaa Dh.D.U.O

Ibsa Ejjannoo Hirmaattota Konfaransii Dhaabbattummaa 7ffaa DhDUO ****** Ummanni Oromoo ummata sirna Gadaa Dimookiraasii bulchiinsa ammayyaa keessatti ilaalamu har’aa ta’e maddisiisee ittiinis kan bulaa ture fi addunyaafis kan gumaachesha. Sirni kun amalasaatiin sirna tokkummaa labsuu fi cimsu waliin jireenya soneessudha. Har’as ta’u, ummanni Oromoo bulchiinsa ammayyaa keessatti mootummaa hundeeffatee hogganamaa bakka jirutti duudhaalee keenya keessatti dhimmoota murteessoo qaama sagantaalee misoomaa, nageenyaafi ijaarsa sirna dimookiraasii, akkasumas, fayyadamummaa ummata Oromoo mirkaneessuurratti tokkummaa ilaalcha cimaa uumuudhaan umurii hiyyummaa gabaasuuf ciminaan hojjetaa jira. Nuti hirmaattonni konfaransii dhaabbatummaa DhDUO 7ffaan konfaransii keenya Onkololeessa 19-23 bara 2010 Adaamaa Galma Abbaa Gadaatti geggeessaa turre milkaa’inaan xummurree jirra. Qaama haaromsa gadi fageenyaa kan ta’e konfaransii dhaabbattummaa kanarratti sochii haaromsa keessatti waa

Naannoleen sadi birrii miliyoona 30 gumaachan

ምስል
Naannoleen Itiyoophiyaa sadi lammiiwwan keenya Naannoo sumaalee irraa buqqaafamaniif birrii miliyoona 30 gumaachan. Deeggarsa maallaqaa kana kan taasisan Naannoo Tigraay,Naannoo Amaaraafi Naannoo Ummattoota kibbaati Ministir di'eetaan waajjira dhimmoota koomunikeeshinii Federaalaa Fireehiwoot Ayyaaleew akka himanitti naannoleen sadeen tokkoon tokkoonsaanii birrii kuma 10 kennan. Kanneen lammiiwwan keenya haala suukaneessaadhaan buqqa'aniif birmatan hundaan galatoomaa jenna!  Read more from Amharic version በኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ለተፈናቀሉ ወገኖች መልሶ ማቋቋሚያ የ30 ሚሊዮን ብር ድጋፍ መደረጉን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የጽህፈት ቤቱ ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አያሌው ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት፤ በቅርቡ በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች በተከሰተው ግጭት ለተፈናቀሉ ወገኖች ማቋቋሚያ የትግራይ፣ አማራና የደቡብ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልሎች ድጋፍ አድርገዋል። ክልሎቹ እያንዳንዳቸው 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታዋ ድጋፉ በብሄራዊ አደጋና ስራ አመራር ኮሚሽን አማካኝነት ለተጎጂዎች እንደሚደርስም አረጋግጠዋል። በአሁኑ ወቅት ከተለያዩ አካባቢዎች ለተፈናቃዮች መቋቋሚያ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው፤