ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የካቢኒያቸውን አዳዲስ እጩ አባላት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቀረቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባሉበት ይቀጥላሉ ያሏቸው የካቢኒ አባላት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የመከላከያ ሚኒስትር አቶ ሲራጅ ፈጌሳ፣ የፌደራል ጉዳዮችና አርብቶ አደር አካባቢ ልማት ሚኒስትር አቶ ካሳ ተክለብርሃን፣ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ አህመድ አብተው፣ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ አብዱልፈታህ አብዱላሂ፣ የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር ይናገር ደሴ፣ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቶ ጌታቸው አምባዬ እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ ናቸው።

አዲስ እየቀረቡ ካሉት እጩ የካቢኒ አባላት መካከል፦
1. ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
2. አቶ ታገሰ ጫፎ፦ የፐብሊክ ሰርቪስ እና ሰው ሀብት ልማት ሚኒስትር
3. ዶክተር አብረሃም ተከስተ፦ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር
4. ዶክተር በቀለ ጉላዶ፦ የንግድ ሚኒስትር
5. ፕሮፌሰር ፍቃዱ በየነ፦ የእንሰሳትና የዓሳ ሀብት ልማት ሚኒስትር
6. ዶክተር ኢያሱ አብረሃ፦ የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ሚኒስትር
7. ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ፦ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
8. አቶ አህመድ ሺዴ፦ የትራንስፖርት ሚኒስትር
9. ዶክተር አምባቸው መኮንን፦ የከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስትር
10. ኢንጂነር አይሻ መሀመድ፦ የኮንስትራክሽን ሚኒስትር
11. ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ፦ የውሃ፣ መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስትር
12. አቶ ሞቱማ መቃሳ፦ የማዕድን፣ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስትር
13. ዶክተር ገመዶ ዳሌ፦ የአካባቢ ደን ልማት እና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር
14. ዶክተራው ሽፈራው ተክለማርያም፦ የትምህርት ሚኒስትር
15. ፕሮፌሰር ይፍሩ ብርሃነ፦ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር
16. ዶክተር ግርማ አመንቴ፦ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ሚኒስትር
17. ዶክተር ሂሩት ወልደማርያም፦ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር
18. ወይዘሮ ደሚቱ ሀምቢሳ - የሴቶች እና ህፃናት ጉዳይ ሚኒስትር
19. አቶ ርስቱ ይርዳው፦ የወጣቶች እና ስፖርት ሚኒስትር
20. አቶ ከበደ ጫኔ፦ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ሃላፊ ሚኒስትር

21. ዶክተር ነገሪ ሌንጮ፦ የመንግስት ኮሙዩንኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሀላፊ ሚኒስትር ናቸው።

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

Ministiroota Itiyoophiyaa har'a muudaman

Ibsa Dhaabbatummaa Dh.D.U.O

Obbo Muktaar Kadir pireezidaantii Mootummaa Naannoo Oromiyaa ta’uun lammata filataman