ልጥፎች

ከኖቬምበር, 2022 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ኢትዮጵያ እንደ ወትሮው የዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በስኬት የማስተናገድ ልምዷን አጠናክራ ትቀጥላለች

ምስል
17ኛው ዓለም አቀፍ የኢንተርኔት አስተዳደር ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የበርካታ ሀገራት ተወካዮች የሚሳተፉበት ይህ ጉባዔ በዚህ ወቅት በኢትዮጵያ መካሄዱ የኢትዮጵያን ገፅታ ለመገንባትና ለዲፕሎማሲው መስክ ልዩ ትርጉም አለው። ኢትዮጵያ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ስሟን ለማጠልሸት ሲጥሩ የነበሩትን አካላት አሳፍራና የተደቀነባትን ፈተና ቀልብሳ ይህንን ዓለምአቀፍ ጉባኤ ማስተናገዷ በፅኑ መሠረት ላይ የቆመ ማንነት ያላት ሀገር ለመሆኗ ማሳያ ነው። ይህ ጉባኤ በኢትዮጵያ እንዳይካሄድ ከፍተኛ ዘመቻዎች ቢካሄዱም በጠንካራ የዲፕሎማሲ ሥራ እና በበሳል አመራር የኢትዮጵያን የአዘጋጅነት ሚና ለማስጠበቅ እና ጉባኤውንም በስኬት ለማስጀመር ተችሏል። ኢትዮጵያ ከጊዜያዊ ችግሮች በላይ የሆነች ባለብዙ ተስፋ ሀገር መሆኗን የዓለም አቀፍ ጉባዔው ታዳሚዎች በተጨባጭ የሚመለከቱበት እና የሚመሰክሩበት አጋጣሚንም ይፈጥራል። የተለያዩ ሀገራት ጠቃሚ ልምዶች የሚቀርቡበት በመሆኑም በኢንፎርሜሽን እና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ላይ ለተሰማሩ አካላት እና ሥራ ፈጣሪዎች ምቹ የልምድ ልውውጥ እና የትስስር መድረክ ነው። በመሆኑም በዚህ ዓለም አቀፍ ጉባኤ የሚታደሙትን እንግዶች በተለመደው ኢትዮጵያዊ የእንግዳ አቀባበል ባህል በማስተናገድ ሁሉም ዜጋ የሀገሩ አምባሳደርነቱን ማስመስከር ይጠበቅበታል። ጉባኤው ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት ለማገዝ የሚያስችል በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለስኬቱ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ መንግስት ጥሪውን ያቀርባል። ኅዳር 20 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

Rakkoon meedaaltuu hawaasa darare furamuu qaba!

Biiroon daldalaa rakkoon medaaltuu/Miizaana hawaasa darare furuudhaaf kan hojjechaa jiru akka ta'e himeera.Biiroon daldalaa Oromiyaa rakkoon madaallii wajjin wal qabatee mudatu furmaata waaraa akka argatuuf hojjechaan jira jedheera.Rakkon safartuu hawaasa miidhamaaf saaxile furmaata waaraa argachuu kan danda'an meeshaaleen meedaallii guutumuudhaan aanaalee hunda yoo dhaqabuu danda'e akka ta'e ogeessi hojii biirichaa tokko himaniiru. Keessumattuu qonnaan bulaan sababa miizanaatiin bu'aa dadhabbiisaa akka hin dhabneef of eeggannoodhaan hojjetamuu qaba.Dallaalaan saamicha bare burjaajessuudhaan qonnaan bulaan akka miidhamu gochuu irraa duubatti hin deebi'u waan ta'eef too'annnoofi hordoffii barbaachisaan taasifamuu qaba. Rakkoon giraama hir'isuudhaan uumamu hawaasa akka hin miine taasisuun kan danda'amu hawaasni fayyadamus waajjiraalee daldalaatiif eeruu kennuudhaaniifi hirmaannaa barbaachisaa taasisuudhaan waan ta'eef  hawaasni faayidaa ofii ka

"አለባብሰው ቢያርሱ...." እንዳይሆን!

ምስል
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ይፋ ያደረጉት የፀረ ሙስና ዘመቻ(እሳቸው ሌባ ማለት ይሻላል ይላሉ) ከዚህ ጋር የሚያያዘውን ያለፈውን ሁኔታ አስታወሰኝ በሽወዳና በማስመሰል በተሞላው የኢህአዴግ ዘመንም በተለያዩ ወቅቶች የፀረ ሌብነት ዘመቻዎች ተጀምረው የሚቋረጡበት የሚዳፈኑበት ሁኔታ እንደነበረ አይተን፤ሰምተን ታዘበናል በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ወቅት በሙስናና ብልሹ አሰራሮች ላይ በአገር አቀፍ ደረጃ በባለሙያዎች የተካሄደው ጥናት ለሕዝብ ይፋ ተደርጎ ዝርዝሩን ሰምተን ወይ ጉድ ብለን ነበር የአሁኑ ዘመቻ በፈራ ተባ እንደማይሆን እንደ ዜጋ ተስፋ አደርጋለሁ በመንግስት በኩል ስራውን የሚመሩ ጠንካራ ሰዎች ያሉበት ኮሚቴ በማቋቋም ቁርጠኝነቱ እንዳለ በይፋ ተረጋግጧል፤የሕዝብ ድጋፍም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ይታመናል በሙሰኞች/ሌቦች ምክንያት ለእንግልት ኑሮ የተጋለጠው የኢትዮጵያ ሕዝብ የመንግስትን ድጋፍና ቁርጠኝነት እንኳን አገኘ እንጂ ሌቦችን አደብ ማስገዛት ያውቅበታል ለማንኛውም በሙስና ክንዱን ያፈረጠመው ኃይል ራሱን ለማትረፍ መንፈራገጡ የማይቀር ነው ለዚህ ደግሞ የገነባው አቅም ያግዘዋል በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ ማለት የሚቻል ቢሆንም “ሆድ ይፍጀው” ብሎ ማለፍ ይሻላል አሁን “ፈረሱም ይኸው ሜዳውም ይኸው” ተብሏልና የመንግስትና ሕዝብ ጠንካራ ቅንጅት በሚያስፈልግበት ወቅት ላይ እንገኛለን፤ሥራው "አለባብሰው ቢያርሱ በአረም ይመለሱ"ዓይነት ነገር እንዳይሆን ብርቱ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል! ኢትዮጵያዬ ችግርሽ ብዙ ነው፤ እንደተለመደው ከችግሮችሽ በላይ እንድትሆኚ ፈጣሪ ይርዳሽ!

Sabdaneessummaan bu'uura Federaalizimii dimokiraatawaa dhugaati

ምስል
Sadaasni 29 guyyaa Ayyaanni Saboota, Sab-lammootaafi Uummattoota Itoophiyaa itti kabajamudha. Bu'uurri kabaja Ayyaana kanaa guyyaa heerri mootummaa FDRI walqixxummaa sabootaa, sablammootaafi uummattoota Itopphiyaa mirkaneesse itti labsamedha. Gaaffiiwwan 1960moota keessa Sochii Barattoota Itoophiyaan gaafatamaa turan gaaffii Lafaafi gaaffii dimokiraasii dabalatee gaaffiin 'Walqixxummaa Sabootaa" tokkodha. Sirni Dargii gaaffii Lafaa deebisuuf yaalus gaaffiin walqixxummaa sabootaafi gaaffiin dimokiraasii deebi'uu hin dandeenye. Kunis uummattoonni Itoophiyaa qabsoo marsaa biraa akka gaggeessan taasise. "Gaaffiin walqixxummaa" saboonni, sablammoonniifi uummattoonni biyyattii mirga walqixxummaan biyya isaanii keessa jiraachuu, afaaniifi aadaa isaanii guddisuufi dagaagfachuu, seenaa isaanii barreeffachuufi qorachuu akkasumas walqixxummaan amantaa akka kabajamu kan akeeku ture. Haata'u malee, gaaffiin kun sirna yeroo sana tureen fudhatama argachuun deebi'uu

አስራ ሁለት ክፍለ ከተሞች የሚኖሩት የሸገር ከተማ መስተዳድር እየመጣ ነው

በአዲስ አበባ ዙርያ ያሉ የፊንፊኔ ዙርያ ልዩ ዞን ስር የነበሩ ሰበታ ፣ ቡራዩ ፣ ለገጣፎ ለገዳዲ ፣ ሱሉልታ እና ገላን ከተሞችን በአንድ ያቀፈ “ሸገር ከተማ” የሚል ስያሜ የተሰጠው የከተማ አስተዳደር  ሊቋቋም መሆኑን ዋዜማ ሰምታለች። በጨፌ ኦሮምያ በቀረበ ሀሳብ መሰረት የተሰናዳው የከተማው መዋቅር የተጠናቀቀ ሲሆን የከተማ ማቋቋሚያው የህግ ሰነድ በጨፌው ሲጸድቅ ወደ ስራ እንደሚገባም ሰምተናል። በአዲሱ የሸገር ከተማ ውስጥ የሚካተቱት አምስቱ ከተሞች እያንዳንዳቸው የከተማ ስያሜ የሚኖራቸው ሲሆን በስራቸው የተዋቀሩ ክፍለ ከተሞች ይኖራቸዋል ። ከተሞቹ በሙሉ የሚመሩት በአንድ ከንቲባ እንደሚሆንም ዋዜማ ከኦሮምያ ክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ሰምታለች። አምስቱ ከተሞችም በጥቅሉ 12 ክፍለ ከተማ ይኖራቸዋል። ቡራዩ እና ሰበታ እያንዳንዳቸው ሶስት ሶስት ክፍለ ከተማ ሲኖራቸው ; ገላን ፣ ለገጣፎ ፣ ለገዳዲ እና ሱሉልታ ደግሞ እያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት ክፍለ ከተሞች እንደሚኖራቸው ዋዜማ  የከተሞቹን ምስረታ ከሚያትተው ሰነድ ተመልክታለች። ለአብነትም ገላን ከተማ ኮዬ ፈጬ እና ገላን የተባሉ ክፍለ ከተሞች ይኖሩታል። ይህ ከተማ የዱከምን የተወሰነ ክፍል ወስዶ የሚዋቀር እንደሆነ ሰምተናል። ሰበታ ደግሞ ገላን ትልቁ ፣ ሰበታና ፉሪ የተባሉ ክፍለ ከተሞች ይኖሩታል። ቀሪ ሶስት ከተሞችም እንዲሁ በክፍላ ከተሞች ይዋቀራሉ። ክፍለ ከተሞቹ እና ከተሞቹ በስራ አስፈጻሚ እና መሰል አመራሮች የሚተዳደሩ ሲሆን ፣ አምስቱ ከተሞች ግን “ሸገር ከተማ”  በሚል ለተሰየመው ከተማ በሚሾመው ከንቲባ የሚተዳደሩ ይሆናል። አዲሱ መዋቅር ያስፈለገው ነባሩ የፊንፊኔ ዙርያ ልዩ ዞን አስተዳደር የከተሞቹን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ባለመቻሉ እንደሆነ አንድ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የኦሮምያ ክልል ባለስል

Muummichi ministiraa Abiy Ahimad Koreen Biyyaalessaa Farra Malaammaltummaa hundaa’uu ifoomsan

ምስል
Muummeen Ministiraa FDRI Abiy Ahimad Koreen Biyyaalessaa Farra Malaammaltummaa hundaa’uu ifoomsaniiru. Muummeen Ministiraa ibsa baasaniin akka beeksisanitti, malaanmaltummaan qiinqanii biyya nyaatu akka ta’ee fi qabeenya bal’aa biyya keenyaa mancaasuun tattaaffii ishee duwwaa hambisuuf, guyyaa fi halkan ilbiisa wasuudha. Aanga’oota namusaa hinqabne, faddaaltotaa fi abbootii qabeenyaa jaalaala qabeenyaan jaamaan wayitaa walta’uun morkatan, duraa buutota hannaa duubaan kan jiran lammiilee hiriirsuu wayita eegalan, malaanmaltummaan qiinqanii ta’ee akka weeraraatti biyya haleela. Haa ta’u malee lafee misooma biyyaa hanga qoqoruutti kan ga’u yoo ta’e malaanmaltummaan weerara ta’eera jechuudha jedhaniiru. Malaanmaltummaan yaaddoo nageenyaa biyya diiguu danda’u ta’uu biyyoonni ragaa bahan bara kana keessaa kan mul’ataan ta’uu ibsuun, baala hadoochituu, kontirobaandii, daddabarsaa seeraan alaa namootaa, daldala seeraan alaa meeshalee waraanaa, daldala waliin dhahuuf, malaanmaltummaa kaayyoo is

ለአማራ ህዝብ ችግር ብዙ አክተሮችን ተጠያቂ ማድረግ እንዳለ ሆኖ ዋናው ችግር ከአብራኩ የወጡ አቀንጭራዎች ናቸው

ባልሆነው ኦሮሙማ እያሉ ማላዘን ትግል አይደለም። ኦሮሙማ የምትለውን ማስፈራሪያ ለግልህ ፍራው። በተለይ በወልቃይት እና ራያ ጉዳይ ኦሮሙማን እንደ መስፈራርቾ ልታመጣው አትችልም። የሰሜኑ ጦርነት ኦሮሙማ ሁለቱን የሰሜን ህዝቦች ለማጠፋፋት የጠነሰሰው ግጭት አድርገህ የምትተነትን ተንታኝ፣ ትን ብሎህ አለመሞትህ የፈጣሪ ድንቅ ስራ መሆን አለበት። ወያኔ በጥጋብ እና በእብሪት የሰሜን እዝን አጥቅቶ የጀመረው ጦርነት ፍጻሜው ቀበቶውን ፈቶ፣ መሬት ልሶ ታረቁኝ እንዲል ሆኗል። አዝናለሁ ምንም ማድረግ አልችልም። የሚታደገው ኃይል ካለ ሊሞክርለት ይችላል። ሐቁ ግን ይኸው ነው። ይኸንን ሐቅ ደግሞ እንመሰክራለን...! ይህን ጦርነት ቀጥ ብሎ የተዋጋው አንተ ጭራቅ አድርገህ ለመሳል የምትሞክረው ኦሮሞ ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር ሆኖ ነው። አንተ ጀግና ብለህ ምስሉን ግድግዳህ ላይ የሰቀልከው አውደልዳይ አንድ ጥይት አልተኮሰም። የክላሽ እና የዲሽቃ ድምፅ መለየት አይችልም። እንዲያው ዝም ስለተባለ ብቻ ሜዳውን ለብቻ ልፏልበት ማለት ነውር ነው። በአንጻሩ አንተ እርኩስ የምታደርገው የኦሮሞ ልጅ ለእናት ሐገሩ በክብር ተፋልሟል። ቆስሏል፣ ደምቷል፣ ተሰውቷል። ይህንን እውነት ባልመሰክር በመንዝ ሸንተረር፣ በአጣዬ ሸለቆ፣ በካሳጊታ ንዳድ፣ በሚሌ በረሃ ወድቀው የቀሩ የኦሮሞ ልጆች አጥንት ይወጋኛል። በደብረታቦር፣ በክምር ድንጋይ፣ በጋሳይ፣ በጉና፣ በወለላ ባህር፣ በደብረዘቢጥ፣ በጋሸና፣ በዳውንት፣ በቀበሮ መስክ፣ በሙጃ፣ በድልብ፣ በድብኮ፣ በጋዝጊብላ፣ በአበርገሌ፣ በወልድያ፣ በመርሳ፣ በኩታበር፣ በቢስትማ፣ በኃይቅ፣ በሲሪንቃ፣ በቆቦ፣ በጎብዬ፣ በተኩለሽ፣ በግራ ካሶ ተራራ የአሞራ ቀለብ ሆነው የቀሩ የኦሮሞ ልጆች አጥንት ይኮሰኩሰኛል። በወቅን፣ በብና ሜዳ፣ በድብ ባህር፣ በዛሪማ፣ በጨው በር፣ በቦ

ብልጭ ብሎ የደበዘዘ ደስታ!

ምስል
የፊንፊኔ/አዲስ አበባ ቀላል ባቡር ግንባታ ተጠናቅቆ ስራውን የጀመረው ከዛሬ ሰባት ዓመታት በፊት ነበር፤በወቅቱ የነበረው የባለስለጣናት ሽር ጉድና የህዝቡ ደስታ በአጠቃላይ የነበረው ሁኔታ ትዝ ይለኛል የባቡሩ መንገድ ተመረቀ በሁለት አቅጣጫዎችም የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ጀመረ ከአያት ጦር ኃይሎችና ከቃሊቲ በመርካቶ ፒያሳ ድረስ በየዕለቱ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ማጓጓዝ ጀመረ ደስ ይላል! በትራንስፖርት ችግር ለእግልት የተዳረጉ የፊንፊኔ/አዲስ አበባ ነዋሪዎች እርካታ በቀላሉ የሚታይ አልነበረም አሳዛኙና ተስፋ የሚያስቆርጠው ጉዳይ ቀስ በቀስ መጣ አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ባቡሮች የፉርጎ እጥረት አጋጠማቸው ተባለ በሁለቱ መስመሮች አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ባቡሮች ግን ልክ እንደ አዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ ሰው በሰው ላይ ተጠባብቆ እያሳፈሩ ስራቸውን እንዲቀጥሉ ተደረገ እነርሱም ከጊዜ በኋላ ወገቤን አሉ እየተመናመኑ ሄዱ መለዋወጫ የለም መጠገን አይቻልም ተባለ በጣም ያሳዝናል!እፎይታ ተሰምቶት የነበረው ተሳፋሪ አዘነ አጉረመረመና ዝም አለ በወቅቱ የነበሩ አመራሮችም እንዲቀየሩ ተደረገ፤በቦታው ብዙ ሰዎች ለአመራርነት መቀያየራቸውን አውቃለሁ ምክንያቱ ለሕዝብ አይነገርም ሚስጢር ሊሆን ይችላል ከሕዝብ ዓይን ሊደበቅ የሚችል ምንም ነገር እንደሌለ ግን ይታወቃል አሁን ባለው ሁኔታ የፊንፊኔ/አዲስ አበባ ቀላል ባቡር አገልግሎት ተቋም ባለቤት የለውም እየተባለ ነው እከሌ ተረክቦ ያስተዳድረው ሲባል ማን ያጨማለቀውን እኔ እረከባለሁ?ዘወር በል!ተብሏል አሉ የፊንፊኔ/አዲስ አበባ ነዋሪ አሁንም በትራንስፖርት አገልግሎት እጦት እየተሰቃየ ነው ጠዋትና ምሽት ላይ ብቻ የነበረው የትራንስፖርት ሰልፍ ቀን ላይም እየታየ ነው(አንዱ የቀድሞ ኢህአዴግ ባለስለጣን በአንድ ወቅት

Waliigaltee nageenyaa mallattaa’een kan injifatte Ityoophiyaadha- Pireezidaanti Saahilawarq Zawudee

ምስል
Waliigaltee nageenyaa mootummaafi ABUT gidduutti mallattaa’een kan injifatte Ityoophiyaadha jedhan Pireezidaantiin FDRI Saahilawarq Zawudeen. Pireezidaanti Saahilawarq waliigaltee nageenyaa mallatteeffame ilaalchisee ergaa dabarsaniin, marii nageenyaa mootummaafi ABUT gidduutti Afrikaa Kibbaatti gaggeeffamaa tureen waliigalteen nageenyaa taasifamuu yaadachiisaniiru. Waliigaltichi Itiyoophiyaafi uummatasheef oduu gaarii ta’uu ibsaniiru. Waliigaltee nageenyaa mallatteeffameen kan injifatte Ityoophiyaa ta’uu ibsuun, waliigalticha hojiitti hiikuun, hojiin deebisanii ijaaruu hojii salphaa akka hin taane nan hubadha jedhan. Itiyoophiyaan kana hundarraa dandamattee sadarkaa guddinaa isheef madaalurra geessisuun nurraa eegama jedhan. Qaamolee nageenyaafi lammiilee biyyattii tokkummaafi nageenya biyyattii kabachiisuuf wareegama kaffalan seenaan kan yaadatu ta’uu ibsaniiru. Ergamaa Addaa Gamtaa Afrikaafi Pireezidaantii duraanii Naayijeeriyaa Oluuseegoon Obbaasaanjoofi Pireezidaantiin duraanii Ke

Afrikaa kibbaatti yaadni Ityoophiyaan dhiyeessite guutummaan guutuutti fudhatameera-Dr. Abiy Ahmad

ምስል
Muummeen Ministiraa FDRI Abiy Ahimad waliigaltee Afrikaa kibbaatti taasifameen yaadni Ityoophiyaan dhiyeessite guutummaan guutuutti fudhatamuu ibsaniiru. Muummeen Ministiraa Abiy Ahimad magaalaa Arbaamincitti haala waqtaawaa irratti ibsa laataniiru. Ibsa isaaniin, waggoota lama dura wanta dhimma hin baafneef obbolaa keenya ajaja kaabaarratti haleellaa suukkanneessaan raawwatera jedhan. Waraanni obbolaa gidduutti qofa osoo hin taane biyyoota kamiinuu gidduutti kan barbaachisuufi deeggaramu miti jedhaniiru. Waraanni jibba kan babl’isu ta’uu ibsuun, waraana baayyee jibbina, nuti kan barbaannu nageenyaafi badhaadhina jedhan. Waliigalteen Afrikaa Kibbaatti taasifameen injifannoon argamuu ibsaniiru. Injifannoo argame keessa inni tokko tokkummaafi birmadummaan Ityoophiyaa qaama kamiinuu waliin mariif kan hin dhiyaanne ta’uu ibsaniiru. Biyya tokko keessa waraanni lama jiraachuu hin qabu dhimma jedhurratti waliigalrteerra gahamuu ibsaniiru. Injifannoon biraa argame naannichatti filannoon ka

የሰላም ስምምነቱን የሚደግፍ ሰልፍ ተካሄደ

ምስል
  በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመውን የግፍ ጭፍጨፋ የሚዘክርና የሰላም ስምምነቱን የሚደግፍ ሰልፍ ተካሂዷል በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመውን የግፍ ጭፍጨፋ ሁለተኛ ዓመት የሚዘክርና በፌዴራል መንግስትና በሕወሓት መካከል የተፈረመውን የሰላም ስምምነት የሚደግፍ ሰላማዊ ሰልፍ በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ነው። “በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግፍ መቼም አንረሳውም”፣የተደረገውን ስምምነት እንደግፋለንና ሁሉም ኢትዮጵያዊ በመከባበርና በፍቅር መኖር አለበት” የሚሉ መልዕክቶች በሰልፉ ላይ እየተላለፉ ይገኛሉ። እንደ ኢዜአ ዘገባ የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍንና የሰላም ስምምነቱ ስኬታማ እንዲሆን በቂ ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባውም ሰልፈኞቹ በያዟቸው መልዕክቶች ጠይቀዋል።

ካናዳ ለስምምነቱ ተፈጻሚነት ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት -ሜላኒ ጆሊ

ምስል
ጥቅምት 24 ቀን 2015 ካናዳ ለሰላም ስምምነቱ ተፈጻሚነት ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን የካናዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሜላኒ ጆሊ ገለጹ። ትናንት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በኢትዮጵያ መንግስትና በህወሓት መካከል የተደረገውን ስምምነት የካናዳ መንግስት እንደሚያደንቅ ገልጸው ስምምነቱ በኢትዮጵያ ሰላም እና ደህንነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን አስገንዝበዋል። በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር ለተደረገው የሰላም ሂደት መሳካት ህብረቱን ጨምሮ በሂደቱ ተሳታፊ ለሆኑ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። ሚኒስትሯ ለሰላም ስምምነቱ መሳካት የካናዳ መንግስት የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማበርከት ዝግጁ መሆኑንም ገልጸዋል።

Joint Statement between the Government of the Federal Democratic Republic of Ethiopia and the Tigray Peoples’ Liberation Front (TPLF)

ምስል
1. As per Article 3 of the Agreement for Lasting Peace and Permanent Cessation of Hostilities, the Representatives of the Government of the Federal Democratic Republic of Ethiopia and the TPLF have agreed to announce to the people of Ethiopia and the rest of the world that after 10 days of intensive negotiations have concluded a peace agreement. 2. We have agreed to permanently silence the guns and end the two years of conflict in northern Ethiopia. 3. The conflict has brought a tragic degree of loss of lives and livelihoods and it is in the interest of the entire people of Ethiopia to leave this chapter of conflict behind and live in peace and harmony.   4. It is fundamental that we reaffirmed our commitment to safeguarding the sovereignty and territorial integrity of Ethiopia and to upholding the Constitution of the Federal Democratic Republic of Ethiopia. Thus, Ethiopia has only one national defense force. We have also agreed on a detailed program of disarmament, demobilization, and

Yaa’iin Dhaabbilee Amantaa Ityoophiyaa waliigaltee taasifame deeggare

ምስል
  Onk24, 2015 Yaa’iin Dhaabbilee Amantaa Ityoophiyaa waliigaltee nageenyaa kan deeggaru ta’uu ibse Yaa’iin Dhaabbilee Amantaa Ityoophiyaa waliigaltee nageenyaa Mootummaa Ityoophiyaafi ABUT gidduutti mallatteeffame kan deeggaru ta’uu ibse. Waliigaltichi barbaachisaa ta’uufi yaa’ichi kan deeggaru ta’uu Barreessaa olaanaan yaa’ichaa Lubni Taagaay Taaddalaa ibsa miidiyaaleef kennaniin himaniiru Milkaa’ina waliigaltichaaf hundi akka tumsu waamicha dhiyeessaniiru. Waliigalticha ilaalchisuun qaamoleen gama miidiyaa hawaasummaan ergaawwan hin barbaachifne tamsaasan gochaa isaaniirraa akka ofqusatan yaadachiisaniiru. Ityoophiyaanonni, dhalattoonni Ityoophiyaafi michuuwwan ishee deeggarsa namoomaa akka taasisaniif waamicha dhiyeessaniiru.

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በተደረሰው ስምምነት ደስታቸውን ገልጸዋል

ምስል
  "ሰላም የንግግር መክፈቻ፣ የኑሮ ቅመም፣ የሰው ልጆች ሕይወታዊ ሀብት ነው" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ጥቅምት 24/2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በተደረሰው ስምምነት ደስታቸውን ገልጸዋል፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመልዕክታቸው "ለእርቅና ለሰላም የምሥራች ያደረሰንን አምላክ እናመሰግናለን" ብለዋል፡፡ በሰላም መወለድ፣ በሰላም መኖር፣ በሰላም መሞት የሰው ልጆች የሚሹት ናፍቆት መሆኑንም ፓትርያርኩ ገልጸዋል፡፡ "ሰላም የንግግር መክፈቻ፣ የኑሮ ቅመም፣ የሰው ልጆች ሕይወታዊ ሀብት ነው" ብለዋል፡፡ ሰላም ለዚህች ዓለም አንድ ዓይን መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ ሰላምን አክብሮ መኖር የሰውነት ግዴታ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ መሪ በዙፋኑ፣ ጳጳስ በመንበሩ፣ ዜጋ በሀገሩ፣ ገበሬ በምድሩ የሚኖረው ሰላም ሲሆን ነው ያሉት ቅዱስነታቸው "የእግዚአብሔር ትልቅ በረከትም ሰላም ነው" ሲሉ ገልጸዋል፡፡ "ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን አሸንፎ በተነሳ ጊዜ የሰበከው ሰላምን ነው" ያሉት ቅዱስነታቸው ሰላም የእኛ ከሆነች ደስታችንና የድካማችን ፍሬ እንበላለንም" ብለዋል፡፡ ጦርነት የሰሙ ጀሮዎቻችን ዛሬ ሰላምንና እርቅን በመስማታቸው ደስታችን ወደር የሌለው መሆኑን ለልጆቻችን እንገልጻለንም ነው ያሉት፡፡ ኢትዮጵያን ከአስከፊ የጦርነት ታሪክ ለማውጣት፣ እግዚአብሔር በሰጣት መልካም ዕድል፣ የተፈጥሮና የሃይማኖት ሃብት እንድታድግ ሰላምን መናፈቅና የሰላም መልዕክተኞች መሆን እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል፡፡ ሐሳብ የበላይ ሲሆን የጦር መሳሪያ

ሁላችንም ሀኪም

ምስል
እናቶች በእንባ እየታጠቡ ተንበርክከው ለመኑ፤’’እባካችሁ በጡታችን ተለመኑ፣ ወደ ጥፋት አትሂዱ፣እርቅ ፍጠሩ፣ሰላም ለሀገራችን አውርዱ ‘’አሉ-መቀሌ ድረስ ተጉዘው፡፡የሀገር ሽማግሌዎችም ’’በኢትዮጵያዊ የሽምግልና ባህላችን መሰረት ተለመኑን፣ለሀገርና ለህዝብ ሰላም ስትሉ አለመግባባታችሁን በውይይት ፍቱ፣ታረቁ ‘’ በማለት ወገባቸው እየተንቀጠቀጠ ለመኑ፡፡የሀይማኖት አባቶች መጽሐፍ ቅዱስና ቁራን ጨብጠው ፊታቸው በመቆም እርቅና ሰላም እንዲያወርዱ ተማጸኑ፡፡ፌዴራል መንገስትም ሰላም እና እርቅ እንዲወርድ በራሱ የዲፕሎማሲ መስመር መለመኑና ማስለመኑ ተነገረ- ’’ተለማማጭ ‘’ተብሎ እስኪተች ድረስ!!ለዚሀ ሁሉ ልመና የተሰጠው ምላሽ ግን እብሪትና ፉከራ ነበር፡፡የፈረደበትን የትግራይን ህዝብ ልጆች ለጦርነት እሳት በመማገድ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ድል ለማግኘት በማለም ዘቻና ማስፈራሪያው በወታደራዊ ትርኢት ታጅቦ ይቀርብ ጀመር፡፡ሳይውል ሳያድርም ራሳቸውን ሲጠብቅ በኖረው የሰሜን ዕዝ ላይ ክህደት በመፈጸም ጨፈጨፉት-ልክ የዛሬ 2 ዓመት፡፡ ተደጋግሞ እንደሚባለውም ኢትዮጵያ የተአምረኞች አገር ናት፡፡ተአምረኛ ልጆቿ በየዘመናቱ በደም በአጥንታቸው ግብር ያስከበሯት ልጆች እናት ነች፡፡ዛሬም በዚህ ተአምረኛ ትውልድ ሌላ ተአምር ተሰራ!!’’እኔ ካልገዛኋትና ካልዘረፍኳት አፈርሳታለሁ ‘’ብሎ የጥፋት ናዳ ያወረደባትንና በታሪኳ ገጥሟት የማያውቀውን እብሪተኛ በደም ግብር አንበርክከው በታሪኩ አድርጎት የማያውቀውን የሰላም ስምምነት እንዲፈርም አደረጉት፡፡የኢትዮጵያንና የህዝቦቿን አንድነትና ሉአላዊነት ሊያከብር፣ለጥፋት የታጠቀውን የጦር መሳሪያ ፈትቶ ለመከላከያ ሰራዊት ሊያስረክብ፣ታጣቂውን ሊበትን….ተስማምቶ በዓለም ፊት ፈረመ፡፡ይህ ድል በዋናነት የትግራይ ህዝብ ድል መሆኑ የሚያጠራጥር አይደለ