የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የአገር ሽማግሌዎች በአዲስ አበባ ይገኛሉ


ዛሬ ከታማኝ ምንጭ ለማረጋገጥ እንደቻልኩት ከሁሉም የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ጎሳዎች የተውጣጡ የአገር ሽማግሌዎች ወደ አዲስ አበባ መጥተዋል

በቁጥር 100 የሚደርሱ የአገር ሽማግሌዎች ወደ አዲስ አበባ የመጡት የክልሉ ርዕሰ መስተዳር በቅርቡ የሰጡትን ሹመት በመቃወምና በጉዳዩ ላይ ከፌዴራል መንግስት ጋር ለመወያየት እንደሆነ ታውቋል

የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሃመድ በቅርቡ ባደረጉት ሹም ሽር የራሳቸውን ጎሳ አባላትና የሚቀርቧቸውን ሰዎች ብቻ ወደ ተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ማምጣታቸውና ይህም የሌሎች ጎሳ አባላትና የክልሉን ሕዝብ ሰሞኑን እንዳስቆጣ ሲነገር ቆይቷል

የክልሉ የአገር ሽማግሌዎች አዲስ አበባ ውስጥ በሆቴል የሚገኙ ሲሆን የዕለት በዕለት የሆቴል ወጪ በመሰቃየት ላይ እንደሚገኙ ታውቋል

ቀደም ሲል የአቶ አብዲ አስተዳደር አንድ ሚሊየን ገደማ ኦሮሞዎች ከጂጂጋና አካባቢዋ እንዲሁም ከሶማሌ ክልልና ኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች በአሳቃቂ ሁኔታ እንዲፈናቀሉ በማድረጉ ሲወቀስ የቆየ ሲሆን ይህም የሆነው የሌሎች ኃይሎችን ጥቅም ለማስጠበቅ ሲባል የተደረገ እንጂ የኦሮሞና የሶማሌ ክልል ሕዝብ እርስ በርሱ በመጠላላቱ እንዳልሆነ እስከ አሁን በመነገር ላይ ይገኛል

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

Ministiroota Itiyoophiyaa har'a muudaman

Ibsa Dhaabbatummaa Dh.D.U.O

Obbo Muktaar Kadir pireezidaantii Mootummaa Naannoo Oromiyaa ta’uun lammata filataman