ልጥፎች

ከኤፕሪል, 2022 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የፌደራል የደህንነትና የጸጥታ የጋራ ግብረ ኃይል መግለጫ

ምስል
      በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጎንደር ከተማ ከቀብር ስፍራ ጋር በተያያዘ በክርስትናና በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የተቀሰቀሰውን ግጭት መነሻ በማድረግ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎችም በሃይማኖት ሽፋን ሁከትና ብጥብጥ በመፍጠር ጸረ-ኢትዮጵያ የሆኑ ሃይሎችን ፍላጎት ለማሳካት በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን የፌደራል የደህንነትና የጸጥታ የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቋል፡፡ የጋራ ግብረ ኃይሉ ዛሬ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ ጸረ ኢትዮጵያ አቋም የሚያራምዱ የተለያዩ የውስጥና የውጭ ኃይሎች ብሔርን መሰረት ያደረገ የጥላቻ አጀንዳ በማሰራጨት ሃገሪቱን ወደ ቀውስ ለማስገባት ጥረት ሲያደርጉ ነበር፡፡ ህብረተሰቡ ለአመታት በገነባው ጠንካራ የሆነ የጋራ እሴት ይህ ሙከራ የከሸፈባቸው ኃይሎች ቀሪውን የሃይማኖት ካርድ በመምዘዝ በተለያዩ እምነት ተከታዮች ዘንድ መጠራጠርና ጥላቻ እንዲፈጠር ብሎም ወደ ግጭት እንዲያመራ በተለያዩ መንገዶች ሲቀሰቅሱ ቆይተዋል ብሏል መግለጫው፡፡ በጎንደር የተከሰተው ግጭት በተለያዩ ዕምነቶች መካከል ግጭት በመቀስቀስ ወደ ሃገራዊ ቀውስ እንዲያመራ የሚደረገው ሴራ አካል መሆኑን ያመለከተው መግለጫው፥ በዚህ ድርጊት በተሳተፉ አካላት ላይ ተገቢ እርምጃ መወሰድ መጀመሩን ጠቁሟል፡፡ በዚህ መሰረት በጎንደር በተከሰተው ግጭት የተሳተፉና ሁከቱን ለማባባስ የተንቀሳቀሱ 280 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን አመልክቷል፡፡ እንደ መግለጫው፥ በጎንደር የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ በሌሎች አካባቢዎችም በተለያዩ እምነት ተከታዮች መካከል ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር የሚጋብዙ ቅስቀሳዎች እንዲሁም ሃሰተኛ መረጃዎችም በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በስፋ

"ከሐሰተኛ የዲጂታል ወያኔ የማኅበራዊ ትሥሥር ገፆች ተጠንቀቁ" - ኢመደአ

ምስል
  ዲጂታል ወያኔ ሕዝብን ከሕዝብ የማጋጨት እና ሀገርን የማተራመስ ተግባሩን የቀጠለ በመሆኑ ኅብረተሰቡ ኮርኳሪ መልዕክቶችን ተጠቅመው የጥፋት ተልዕኮ ይዘው ከሚመጡ ሐሰተኛ የማኅበራዊ ትሥሥር ገፆች ሊጠነቀቅ እንደሚገባ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አሳሰበ። ዲጂታል ወያኔ ከአካላዊ ጦርነቱ አስቀድሞ ኢትዮጵያውያንን ለማባላት፣ ለማጋጨት እና እኩይ ተግባሩን ለማስፈፀም የተለያዩ ትርክቶችን እየፈጠረ እኩይ ተግባራትን ሲያከናውን የቆየ እና አሁንም በዚህ ተግባሩ እንደገፋበት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሹመቴ ይግዛው ገልጸዋል። እንደ ዶ/ር ሹመቴ ገለጻ፣ ባለፉት 30 ዓመታት የተሠሩ የፖለቲካ ትርክቶች እና ሴራዎች ለማኅበራዊ ትሥሥር ገፆች ትልቅ ግብዓት ወደ መሆን አዝማሚያ ሄደዋል። ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም አሸባሪው ሕወሓትን ጨምሮ በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ወጪ ያሉ የኢትዮጵያን መልካም ነገር የማይፈልጉ አካላት በዲጂታል መንገድም ሆነ በአካላዊ ጦርነት ኢትዮጵያን ለማጥቃት ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ። ዲጂታል ወያኔ የዲጂታል ጦርነቱን በተለያየ መንገድ እየተገበረ መሆኑን ገልጸው፣ ለአብነትም ኦሮሞ ሳይሆኑ የኦሮሞ ስም ገፆችን በመክፈት፣ አማራ ሳይሆኑ የአማራ ስም የያዘ ገፅ በመክፈት የብሔር ጉዳዮችን አንስቶ በመሳደብ እና ተቆርቋሪ በመምሰል በሐሰተኛ ገፅ ተጠቅመው ከፍተኛ የሆነ የመረጃ ማዛባት ጦርነት እያካሄዱ ነው ብለዋል። ከ800 ሺህ በላይ ሐሰተኛ ማኅበራዊ የትሥሥር ገፆች ተከፍተው ሀገርን ለማተራመስ እየሠሩ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል። ቁጥራቸው በርከት ያለ የሐሰተኛ መረጃ አሠራጮች እና የሐሰተኛ ገፅ ተጠቃሚዎች በክስ ሂደት ላይ እንዳሉ ተነግሯል። ዋናው ነገር ከገበያ የተገኘ ሁሉ እንደማይገዛ እንዲሁ መረጃዎች ሁሉ አይገበ

ወደ ሃገራቸው ያልተመለሱ ጥቂት የሠራዊት አባላትን አሰመልክቶ የተሠጠ ማብራሪያ

ምስል
  በዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ተሠማርተው ወደ ሃገራቸው ያልተመለሱ ጥቂት የሠራዊት አባላትን አሰመልክቶ የተሠጠ ማብራሪያ:- አሸባሪው የህወሃት ቡድን የሃገር ሉአላዊነት ምሽግ የሆነውን መከላከያ ሠራዊት በመምታት ለውጡን ቀልብሶ ወደ ስልጣን በመመለስ ኢትዮጵያን መግዛት፤ መግዛት ካልቻለ የራስን ዕድል በራስ መወሰን በሚል ክልሎችን በመገነጣጠል ኢትዮጵያን የማፍረስ ዓላማ ይዞ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በሠሜን ዕዝ ሰራዊታችን ላይ ጥቃት ከፈተ፡፡ አሸባሪው ቡድን በሠሜን ዕዝ ሰራዊታችን ላይ ጥቃት ከመፈፀሙ አስቀድሞ በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ የሚገኙ ትግርኛ ተናጋሪዎችን "ኢንፍልትሬት" በማድረግ (ሰርጎ በ መግባት) ለእኩይ አላማቸው በማዘጋጀት የሠሜን ዕዝ መከላከያ ሠራዊታችን ላይ ጥቃት በመክፈት ሠራዊታችንን ከውስጥና ከውጭ እንዳጠቃ ይታወቃል፡፡ የህግ ማስከበርና የህልውና ዘመቻው ሲጀመር ከመከላከያ ሰራዊታችን ጋር አብረው ሲሰሩ የነበሩ ከወታደር እስከ ከፍተኛ አመራር ያሉ ትግርኛ ተናጋሪዎች ለዘመቻው ስኬትና እርስ በእርስ እንዳንማታ ሲባል ደመወዝና ቀለባቸው ሳይቋረጥ በቤታቸው እንዲቆዩ መደረጉ ይታወቃል፡፡ ከሰሜን ዕዝ ጥቃት በፊት ወደ ውጭ ሀገር ሰላም ለማስከበር የተላኩ ትግርኛ ተናጋሪዎች ግን በሰራዊታችንና በተልዕኮው ላይ ችግር አይፈጥሩም በሚል በስራቸው እንዲቀጥሉ ተደርጓል፡፡ ሆኖም ግን ህወሃት የትግርኛ ተናጋሪዎች ወደ ሀገራቸው እንዳይመለሱ በውጭ በሚገኙ የወያኔ ቅጥረኞች የሃሰት ፕሮፖጋንዳ በመነዛቱ በአባላቱ ላይ ውዥንብር ፈጥሯል። ሃገር ቤት ከተመለሳችሁ ትታሰራላችሁ የሚል የማስፈራሪያ ውሸት በመንዛትና በዘረኝነት በመቀስቀስ አገራቸውንና ተቋማቸውን ሲያገለግሉ የነበሩ የትግራይ ተወላጅ የሠራዊት አባላትን የማስኮብለል ስራ ተሰርቷል

‘Yaa Marqaa si afuufuun silqimsuufi’

ምስል
  Shirri wayyaanee dhuma hin qabu.Hoggantoonni garee shororkeessaa wayyaanee shira omishaa oolanii bulu.Shira faayidaasaanii eegsisuuf yeroo himan xiqqumallee hin qaana’an.Faayidaasaanii kan eegsisuuf akka ta’e mirkaneeffannaan battalatti ifoomsu. Kaleessas akkuma baran shira faayidaa keenya nuuf eegsisa,gara Finfinneettis akka deebinuuf haala nuuf mijeessa jedhanii yaadan nutti himaniiru.Sanuu ibsa affaan Ingliiziitiin baasaniin Ummata Oromootiif aantummaa akka qaban odeessan.Oromoon gowwaadha,waan nuti jenne hunda fudhatee hojiirra oolcha jedhanii yaadan.Gamni isaan malee kan biraa addunyaa kana irra hin jiru. Waan Saba Oromoo irratti raawwachaa turan dagachuudhaan amma Saba Oromootiif aantummaa akka qaban himan.Mummicha ministiraa Itiyoophiyaa Dr.Abiy Ahmad jibbuudhaan Saba Oromoon jaaladha jechuun sobadha.Soba Wayyaanee kana kan fudhatu diina Saba Oromooti. Bara wayyaaneen waggoota 27 guutuu taayitaa irra turtetti dararama guddaa kan arge,miidhaa gareen shororkeessituun t

‘Soba adii Getaachoo Raddaa’-Dr.Laggasa Tulluu

ምስል
  Ministirri tajaajila komunikeeshinii Mootummaa Dr.Laggasa Tulluu Ob.Getaachoo Raddaa Naannoo Affaar keessaa guutummaatti baaneerra jechuun kan ibse soba adiidha jedhaniiru. Oduu himaan garee shororkeessaa Getaachoo Raddaa ibsa kaleessa Rooyitarsiif kenneen Naannoo Affaar keessaa guutummaatti baaneerra jechuunsaa gabaafamaa ture. Hidhattoonni garee shororkeessaa Irrabtii keessaa saamicha raawwachuun ba’e malee aanaalee naannoo Affaar kanneen biroo humnaan qabatan keessaa hin baane jedhaniiru Dr.Laggasan Guutummaatti baasuu miti,inumaatuu iddoowwan tokko tokkoon hidhattoota isaanii dhiyeessaa jiru jedhan ministirichi. Hawaasa idil Addunyaafi jiraattoota naannoo Tigraay burjaajessuuf ololaa jiru malee aanaaleen Affaar humna shororkeessaadhaan qabaman gadi hin lakkifamne jedhaniiru ministirichi. Hawaasa isaaniitiif yaadu yoo ta’e iddoowwan waldhabdeedhaaf haala mijeessan keessaa ba’uu akka qabaniifi hawaasni idil addunyaatis dhibbaa taasisuu akka qabu ministirichi dubbataniiru.

'Antooniyoo Gutereez Xalayaa Dabratsiyoon dubbisuu hin qaban'

ምስል
  Itaamaazyooriin waliigalaa humnoota waraanaa Itiyoophiyaa Fiild Maarshaal Birhaanuu Juulaa Barreessaan dhaabbata mootummoota gamtoomanii Antooniyoo Gutareez Xalayaa dura taa’aa TPLF’fiin ergameef dubbisuu hin qaban jedhan Dhaabbanni mootummoota gamtoomanii Mootummaan Itiyoophiyaa utuu jiruu garee shororkeessaa TPLF wajjin walitti dhufeenya qabaachuun sirrii miti kan jedhan Fiild Maarshaal Birhaanuu Juulaa dhimmi Janaraal Tsaadiqaan Gabratinsaay ana wajjin dhimmoota gara garaa irratti akka mari’anne fakkeessuudhaan kan odeessan dhiphina keessa isaaniitti uumametti fala barbaaduuf tooftaa mijeeffatan akka ta’e dubbataniiru. Fiild Maarshaal Birhaanuu Juulaa turtii galgala kana ‘EMS Eletawi’ wajjin bilbilaan You tube irratti marii kallattii irratti taasisaniin dhimmoota hedduu irratti ibsa kenuudhaan ololaafi shira beekamaa wayyaanee irratti iftoomina uumaniiru.

በወቅታዊ ሀገራዊ የደህንነትና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ በመምከር፣ የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤቱ የሰጠው መግለጫ

ምስል
  የተከበራችሁ የሀገራችን ሕዝቦች፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ የደረሰችው በየዘመናቱ የገጠሟትን ፈተናዎች በድል እየተሻገረች ነው። እንድትጠፋ የሚፈልጉ ኃይሎች ሊያጠፏት ሲነሡ ምንጊዜም ሦስት ኃይሎችን እንደሚጠቀሙ እሙን ነው። የመጀመሪያዎቹ ምንጊዜም የማይተኙት ታሪካዊ ጠላቶቻችን ናቸው። እነዚህ ጠላቶቻችን ጠላትነታቸውን የሚያቆሙት ኢትዮጵያ የምትባለው ሀገር ከምድር ገጽ ስትጠፋ ብቻ ነው። ይኼ ምኞታቸው እንዲሳካ ብቻቸውን አይሠሩም። ተላላኪ አላቸው። እነዚህም ሁለተኛዎቹ ናቸው። ለገንዘብና ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ወገናቸውን እንደ ይሁዳ የሚሸጡ፣ ሀገር የጣለባቸውን እምነት በሽርፍራፊ ሳንቲም የሚለውጡ ሀገር አልባ ባይተዋሮች ሞልተዋል። የተናገሩትን ሆነው የማይገኙ፣ ቀን ቀን በአደባባይ ስለ ሕዝብ ፍቅር እና ስለ ሀገር አንድነት የሚደሰኩሩ፤ ማታ ማታ ከጠላት ጋር እያሴሩ ወገንን የሚክዱና ሀገር ለማፍረስ ጉድጓድ የሚቆፍሩ ናቸው። ሦስተኛዎቹ የኢትዮጰያ ጠላቶች ደግሞ ባለማወቅ የእነዚህ የሁለቱ አካላት ተባባሪ የሚሆኑት ናቸው። ግዴለሽ ስለሆኑ፣ የሚያደርጉት ነገር የሚያስከትለውን ውጤት ሳይገምቱ እንዲሁ በነሲብ የጠላትን ተልዕኮ የሚፈጽሙ ውል አልባ ኢትዮጵያውያን ናቸው። እነዚህ ኢትዮጵያውያን አንድን ነገር ተቀብለው ማውራታቸውን፤ ወይም አድርጉ የተባሉትን ነገር ማድረጋቸውን፤ ወይም ሳይመረምሩ የሰጧቸውን መረጃ ሁሉ ማስተላለፋቸውን እንጂ በሀገራቸውና በሕዝባቸው ላይ የሚያስከትለውን ጣጣ አይመረምሩትም። ከመረመሩም ጉዳቱ ከደረሰ በኋላ ብቻ የሚፀፀቱ ናቸው። ኢትዮጵያ ይበልጥ እየተፈተነች ያለችው በእነዚህ በሁለቱ ነው። ታሪካዊ ጠላቶቻችን በአንድ ስሙ ቁርጣቸው የታወቀ ጠላቶቻችን ናቸው። ባይተዋሮችና ውል አልባ ኢትዮጵያውያን ግን በወቅቱ ልብ ሳንላቸው ደጋግመው ዋጋ ያስከፍሉናል።

አሸባሪው ሸኔን የማፅዳቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስታወቀ

ምስል
  አሸባሪውን ሸኔ ከተለያዩ አካባቢዎች የማፅዳቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስታወቀ፡፡ የክልሉ መንግስት ጉዳዩን አስመልክቶ ትናንት ባወጣው መግለጫ፥ ሸኔ ባለፉት አራት ዓመታት በኦሮሞ ህዝብ ላይ የፈጸመው አስነዋሪ እና ጭካኔ የተመሞላበት ተግባር ቡድኑ ምንም አይነት የፖለቲካ አላማ እና ግብ እንደሌለው ማሳያ መሆኑን አንስቷል፡፡ ሰሞኑን በሽብር ቡድኑ ላይ የተቀናጀ እርምጃ እየተወሰደበት መሆኑን የጠቆመው መግለጫው፥ ይህን ተከትሎም ጊዜ ያለፈባቸው የቡድኑ አመራሮች በሰው ልጅ ላይ የማይደረግ ድርጊት በኦሮሞ ህዝብ ላይ ሲፈጽሙ መቆየታቸውን በራሳቸው ላይ መመስከር መጀመራቸውን አመላክቷል፡፡ የሰላም ጥሪ የተቀበሉ ወጣት የሽብር ቡድኑ አባላትም ሰላማዊ መንገድን መርጠው በብዛት እጃቸውን እየሰጡ እንደሚገኙም ነው የጠቆመው። የኦሮሞ ህዝብ ጥቅም በጠመንጃ አፈሙዝ ሳይሆን በሃሳብ ልዕልና የሚከበር መሆኑን በመጠቆም ፥ መንግስት ቡድኑ በሰላማዊ መንገድ እንዲታገል ሰፊ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱ ተገልጿል፡፡ ሸኔ ከመንግስትም ባለፈ ከመላው ኦሮሞ ህዝብ የሰላም ጥሪ ሲቀርብለት የቆየ ቢሆንም፥ቡድኑ የተቀበለውን የባንዳነት ተልዕኮ ለማሳካት እና የኦሮሞን ፖለቲካ ለመቀልበስ ቀን ከሌት የጠላትነት ተግባር መፈጸሙን ቀጥሎበታል ነው ያለው መግለጫው፡፡ በዚህ ምክንያት የኦሮሞ ህዝብ ባለፉት አራት አመታት በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የጭካኔ ተግባር ሲያስተናግድ ቆይቷል ፤ በዚህም ሸኔ ከኦሮሞ ህዝ