ሕወሓትን ይደግፋሉ ተብለው ተዘግተው የነበሩ ሆቴሎች ተከፍተው ብድር ተመቻቸላቸው

 



የወንጀል ምርመራ ደቱ እንደሚቀጥል ፍት ሚኒስቴር አስታውቋል

በሽብርተኝነት የተፈረጀውን ሕወሓ ይደግፋሉ ተብለው ከስምንት ወራት በላይ ተዘግተው የቆዩት ሆቴሎች በአነስተኛ ወለድ ብድር እንደተመቻቸላቸው የኢትዮጵያ ሆቴልና ማርኬቲንግ በር አስታወቀ፡፡

ሆቴሎቹ በዋነኝነት ገንዘብ በማሸሽ፣ ጦርነ ወቅት ከሕወሓት ጎን በመሆን በፋይናንስ  በማገዝ በመሳሰሉ ጉዳዮች በመጠርጠራቸው ታሽገው ቆይተዋል፡፡ ከስምንት ወራት በላይ ለሆነ ጊዜ አገልግሎታቸውን ሙሉ በሙሉ አቋርጠው የቆዩት ሆቴሎቹ 2,000 በላይ ራተኞች እንዳሏቸውና ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ወደ አገልግሎት መመለሳቸው ታውቋል።

ተዘግተው ከነበሩት ያህል ሆቴሎች መካከል ካሌብ ሆቴል፣  አክሱም ሆቴል፣ ሆሊዴይ ሆቴል፣ ሐርመኒ ሆቴልና አዲሲኒያ ሆቴል ይገኙበታል፡፡ የአዲሲኒያ ሆቴል ባለቤት / ዲስ ገብረ ማርያም ሆቴሉ ተዘግቶ በቆየበት ወቅት ከፍተኛ ኪሳራ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ 

በተለይም ከአፍሪካ ብረት ጉባ ያስፖራ ወደ ገር ቤት መምጣት ጋር ተያይዞ የሆቴል ዘርፉ መነቃቃት ያሳየበት ጊዜ ቢሆንም ሆቴላቸው አገልግሎት ባለመስጠቱ ተጠቃሚ መሆን አለመቻሉን ገልጸዋል።

አዲሲኒያ 120 በላይ ራተኞች እንዳሉት የገለጹት / ዲስ ራተኞቹን መወ መክፈል የቻለው ሆቴሉ ከታሸገበት ጊዜ በኋላ ባለው አንድ ወር ብቻ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ውጪ የቆዩት ራተኞች ሆቴሉ መከፈቱን ተከትሎ ወደ ራቸው ተመልሰዋል ብለዋል።

የሆሊዴይ ሆቴል ማናጀር አቶ ፍቃዱ አብረሃም በበኩላቸው ሆቴሉ ተዘግቶ በቆየባቸው ስምንት ወራት ውስጥ የነበረውን ደንበኞች በማጣቱ በድጋሚ ደንቦኞቹን ለማግኘት ፈታኝ እንዳደረገበት ገልጸዋል፡፡ በአገልግሎት ዋጋም ላይ ከቆዩ ሆቴሎች ጋር ሲነፃፀ ዝቅተኛ ሲሆን ማስተካከያ ለማድረግም መቸገሩን አስረድተዋል፡፡

የመደበኛ ብድርም ሆነ በኮቪድ-19 ወቅት የተበደሩት ብድር ተደራራቢ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን የገለጹት አቶ ፍቃዱ የብድር ማራዘሚያ ጥያቄያቸው ተቀባይነት ባለማግኘቱ ንብረት ሸጠው መክፈላቸውን አክለዋል፡፡ ሆሊዴይ ሆቴል 100 በላይ ራተኞች ያሉት አሁን በድጋሚ ወደ አገልግሎት ሲገባ ራተኞቹ ጥሪ ማድረጉን ገልጸዋል።

ሆቴሎቹ ለበርካታ ጊዜያት ተዘግተው በመቆየታቸው የደረሰባቸውን ኪሳራ ታሳቢ በማድረግ ከብራዊ ባንክ ጋር በመነጋገር ብድር እንደተመቻቸላቸው የኢትዮጵያ ሆቴልና ቱሪዝም በር ፕሬዳንት አቶ ጌታሁን ለሙ ገልጸዋል፡፡ በአነስተኛ ወለድ የተዘጋጀው ብድር በተለይም ተዘግተው በመቆየታቸው ራተኞች መወ መክፈል ያልቻሉ ሆቴሎችን ማስኬጃነት እንዲጠቀሙበት ለማገዝ የታሰበ መሆኑን አክለዋል፡፡

ብድሩ 5.5 በመቶ ወለድ የተሰጠ መሆኑን፣ ለእያንዳንዱ ሆቴል አምስት ሚሊየን ብር እንዲሰጥ መወሰኑን ገልጸው የመመለሻ ጊዜውን ከአንድ መት ተኩል እስከ ሁለት መት እንደሚሆን አስረድተዋል፡፡  

ሕወሓትን ይደግፋሉ ተብለው የተጠረጠሩትን ሆቴሎችን ጉዳይ የሚከታተለው ፍትሕ ሚኒስቴር እስካሁን ውሳኔ አልሰጠም፡፡ ሆቴሎቹ ለአገልግሎት ክፍት ቢሆኑም የወንጀል ተሳትፏቸው በምርመራ ላይ መሆኑንና ደቱም እንደሚቀ የፍት ሚኒስትር ኤታው አቶ ቃዱ ፀጋ ተናግረዋል ማስተዳደር መቆጣጠርም ሆነ ማሸግ ውስጥ ፍትሕ ሚኒስቴር ተሳትፎ እንደሌለው አክለዋል፡፡

@Reporter

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

Ministiroota Itiyoophiyaa har'a muudaman

Ibsa Dhaabbatummaa Dh.D.U.O

Obbo Muktaar Kadir pireezidaantii Mootummaa Naannoo Oromiyaa ta’uun lammata filataman