ልጥፎች

ከሜይ, 2016 ልጥፎች በማሳየት ላይ

“ይሉሽን በሰማሽ ገበያ ባልወጣሽ” አለ ያገሬ ሰው

ምስል
ጀዋር መሃመድ ዛሬ በጣም ተደስቷል፤እጀግ በጣም ደስ ብሎታል ፍንድቅድቅ ስለማለቱም በገፁ ላይ ዛሬ የለቀቃቸው የሃሰት መረጃዎች ያመለክታሉ “አንዳንዶች የ12ኛ ክፍል ፈተና መለቀቁ ሞራላዊ አይደለም፤ለኦሮሚያ ተማሪዎች መድሎ ለፍጠር ታስቦ ነው ማለት ይቃጣቸዋል።ለመሆኑ አምስት ወር ሙሉ ትምህርታቻውን ያልተከታተሉ በወያኔ ወድታደሮች ሲገደሉና ሲንገላቱ የከረሙ ተማሪዎችን ከሌሎች እኩል መፈተንስ ሞራላዊ ነው?ለኦሮሚያ ተማሪዎች መድሎ ማድረግ አስበን ቢሆን ኖሮ ውስጥ ለውስጥ ማከፋፈል ይቻል ነበር።ነገር ግን ፈተናውን በግልጽ ለሁሉም ሊደርስ በሚችል ሁኔታ ነው የተበተነው።ምክንያቱም አላማው ትምህርት ሚኒስቴር ይህን ፈተና ሰርዞ ለተማሪዎች በቂ ጊዜ ሰጥቶ አዲስ ፈተና እንዲያዘጋጅ ታስቦ ነው” ይለናል ጀዋር ለኦሮሞ ልጆች አሳቢና ተቆርቋሪ መሆኑን ለማሳየት ጀዋር መሃመድና ተከታቹ በኦሮሞ ልጆችና በሌሎች የኢትዮጵ ልጆች ላይ ይቅርታ የሌለው ክህደት ፈፅመዋል የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ሲባል የተማሪዎችን የአመታት ልፋት ፉርሽ ማድረግ ጀዋርና መሰሎቹን ተጎጂ እንጂ ተጠቃሚ ማድረግ አይችልም ፈተና ተሰረቀ ሌላ ፈተና ተዘጋጅቶ የኦሮሞም ሆኑ ሌሎች የኢትዮጵያ ተማሪዎች ተፈትነው ወደ ቀጣይ የትምህርት ደረጃ ይሸጋገራሉ ቆዳን ለመዋደድ መፍጨርጨር የትም አያደርስም የኦሮሞ ሕዝብም ሆነ ልጆቹ በኦሮሞ ስም የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት የሚሯሯጡትን አብጠርጥረው ያውቃሉ

Barreeffama haala yeroo irratti ejjannoo Mootummaa Naannoo Oromiyaa balballoomsu

ምስል
“Gochaan hanna qormaata biyyaalessaa raawwatame gantummaa biyyaafi  egeree dhaloota borii irratti yakka aggaamemedha!” Seenaa biyya keenyaa keessatti duubatti hafummaafi wallaalummaan godaannisni ummata keenyarratti gatanii darban qabsoo har’a deega maqsuu dabalatee gageessaa jirru daran dhimmoota ulfaataa taasisan akka ta’e ummatni naannoofi biyya keenyaa haalaan hubatu.  Mootummaan sirna federaalawaa dimokraatawaafi misoomawaa yaa ta’uu ummataafi heeraan ijaarame fedhiifi faayidaa ummattoonni biyya keenyaa sirna dimokraasii keessatti argachuu barbaadan kan ittiin ibsataniifi mirkaneeffatanis godaannisa kana hundeerraa dhabamsiisuuf akka ta’e beekamaadha. Waggoottan 25’n dabran keessa mootummaan Naannoo Oromiyaas ta’e biyya keenyaa jijiiramni bu’uraa damee barnootaarratti fiduudhaaf tattaafiin taasisaniifi bu’aa ba’iin keessa dabarsan hangam takka wareegama akka gaafate ragaan ummata naannoo keenyaati.Hooggansi damee barnootaa kennamaa ture bu’uraalee misoomaa damichaa ba

Ibsa ejjennoo mootummaa Naannoo Oromiyaa

ምስል
Haala yeroo irratti ibsa ejjennoo mootummaa Naannoo Oromiyaa balballoomsu “Qormaata biyyaalessaa olola hintaaneen gufachiisuuf yaaluun dorgomummaa sirna federaalizmii keessatti ummatni Oromoo qaburratti haleellaa aggaameedha” Biyyi keenya biyya waggoota dheeraadhaaf saboonni sablammooniifi ummatoonni ishee cunqursaa hammaataa,duubatti hafummaafi hiyyummaa keessatti kufanii itti turanidha.Keessaahuu ummatni Oromoo cunqursaa dachaa irra tureen, eenyummaan sbummaasaa dhokatee biyya ofiisaa ijaare keessatti akka lammii lammaffaatti akka ilaalamu sirna gita bittoota nafxanyaatiin itti murtaa’e ture.  Carraa barnootaa akka hin arganne karaa hundaan karra itti cufaa kan turan sirnootni kun ummatni kun dammaqinni sammuusaa yoo dabale isaaniif  sodaa akka ta’e yeroo addaddaa ifatti kaasaa turan. Sirna cinqursaa kana yeroo dhumaaf dhabamsiisuuf Qabsoon ummatni Oromoo sabootaafi sablammoota biroo wliin taasise injifannoodhaan xumuramee Caamsaa 20/19883 irraa kaasee gaaffileen gama

አይሞቀው አይቀዘቅዘው ባለስልጣን ይዞ የህዳሴ ጉዞ?

ለእኔ እንደሚመስለኝ አይሞቀው አይቀዘቅዘው ባለስልጣን ይዞ መቼም ቢሆን የትም መድረስ አይቻልም የአገራችን ስርዓት አደጋዎች በአግባቡ ተለይተው ታውቀዋል እነዚህ አደጋዎች ኪራይ ሰብሳቢነት፤አክራሪነትና ሽብርተኝነት እንዲሁም ጥበትና ትምክህተኝነት ተብለው ተለይተዋል ከእነዚህ ውጭ ያሉቱ እዳቸው ገበስ ነው ሁሉንም በማሳተፍና ተጠቃሚ በማድረግ በቀላሉ መፍትሄ ማግኘት የሚችሉ ናቸው ለማለት ነው አፅንኦት ተሰጥቷቸው የተለዩ አነዚህ የስርአታችን አደጋዎች ግን ተወግደው ከአሳሳቢነት ደረጃ መውጣት የሚችሉት የሁሉም ወገኖች ያላሰለሰ ጥረት ሲኖር ብቻ እንደሆነ ሊታወቅ ይገባል አለበለዚያ በተወሰኑ አካላት ጩኸትና ነጋ ጠባ ማላዘን ችግሮቹ ዘላቂ መፍትሄ ማግኘት አይችሉም በተለያዩ የኢህአዴግ ሰነዶች ላይ እንደ ተብራራውና በመድረኮች ላይም አፅንኦት ተሰጥቶት እንደሚነገረው የተጠቀሱት የስርአታችን አደጋዎች ማለትም ኪራይ ሰብሳቢነት፤አክራሪነትና ሽብርተኝነት እንዲሁም ጥበትና ትምክህተኝነት በአመለካከትም ሆነ በድርጊት ደረጃቸው ይለያይ እንጂ በሁሉም ውስጥ አሉ ይህ ማለት ችግሮቹ በህብረተሰብ፤በድርጅትና በመንግስት ውስጥ ይገኛሉ ማለት ነው መቼም እኔ ፍፁም ነኝ ከእነዚህ አሳሳቢ ችግሮችም ነፃ ነኝ ብሎ የሚከራከር የሚኖር አይመስለኝም የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ድርጊት የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ውስጥ ስለመኖሩ ጉቦ መስጠትና መቀበል፤በአቋራጭ ተጠቃሚ ለመሆን እስኪሰባበሩ መሯሯጥና የመሳሰሉ ህገ ወጥ አካሄዶች በተጨባጭ መኖራቸው በግልፅ የሚታዩ ቀላል ማሳያዎች ናቸው የጠባብነትና የትምክህተኝነት አደጋዎችም በተወሰኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ብቻ ሳይሆን እዚህም እዚያም እንዳሉ በተጨባጭ ተረጋግጧል በተግባር ተገልጦ ያየነውና የሰማነውም ይኸው ነው ጠባብ ኦሮ

OMN: Sagalee Kaabinee OPDO dhooysaan waraabamee OMNif Ergamee.

ምስል
ዛሬ ትናንት አይደለም የደርግ ስርዓት መውደቂያ ሲቃረብ እንዲህ ሆኖ ነበር የስርአቱ ሰዎች ተስፋ ቆረጡ፤አንድ ሰውና አንድ ጥይት እስኪቀር ድረስ ወይ ፍንክች ብሎ  ሲፎክር የቆው ሰውዬም ወደ ዚምባብዌ ፈረጠጠ የውስጥ ቦርቧሪዎችም የሚችሉትን ሁሉ አደረጉ ሚስጢር ዘረገፉ ለተቀናቃኝ ኃይልም አሳልፈው ሰጡ ዛሬም በዚህ መንገድ ሊሳካልን ይችላል ያሉ ወገኖች በስልቱ ለመጠቀም በመሞከር ላይ የሚገኙ ይመስላል ሰሞኑን እንዲህ ሆነ አቶ ፈቃዱ ተሰማ የተባሉ አንድ የኦሮሚያ  ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ባልስለጣን በአንድ መድረክ ላይ ከመልካም አስተዳደር ጋር ተያይዞ ከሕዝብ ለሚነሱ ቅሬታዎች አስቸኳይ ምላሽ እየሰጠን አይደለም የሚል ወቀሳ አሰሙና በየዘርፉ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ጠቃቅሰው በርትተን መስራት ይጠበቅብናል የሚል ጠንከር ያለ ይዘት ያለው መልዕክት አስተላለፉ ጀዋር መሃመድ ደግሞ ይቺ ለአምስተኛው ዙር የብጥበጣ ፕሮግራም ስኬት ታግዛለች በሚል ከንቱ ተስፋ በድብቅ ተቀርፆ የተላከልን ነው እስኪ እንኩና ተነሳሱ ሲል ለተከታዮቹ አቀረበ እንግዲህ ዛሬ  ትናንት አይደለም

ዛሬ ትናንት አይደለም

የደርግ ስርዓት መውደቂያ ሲቃረብ እንዲህ ሆኖ ነበር የስርአቱ ሰዎች ተስፋ ቆረጡ፤አንድ ሰውና አንድ ጥይት እስኪቀር ድረስ ወይ ፍንክች ብሎ  ሲፎክር የቆው ሰውዬም ወደ ዚምባብዌ ፈረጠጠ የውስጥ ቦርቧሪዎችም የሚችሉትን ሁሉ አደረጉ ሚስጢር ዘረገፉ ለተቀናቃኝ ኃይልም አሳልፈው ሰጡ ዛሬም በዚህ መንገድ ሊሳካልን ይችላል ያሉ ወገኖች በስልቱ ለመጠቀም በመሞከር ላይ የሚገኙ ይመስላል ሰሞኑን እንዲህ ሆነ አቶ ፈቃዱ ተሰማ የተባሉ አንድ የኦሮሚያ  ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ባልስለጣን በአንድ መድረክ ላይ ከመልካም አስተዳደር ጋር ተያይዞ ከሕዝብ ለሚነሱ ቅሬታዎች አስቸኳይ ምላሽ እየሰጠን አይደለም የሚል ወቀሳ አሰሙና በየዘርፉ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ጠቃቅሰው በርትተን መስራት ይጠበቅብናል የሚል ጠንከር ያለ ይዘት ያለው መልዕክት አስተላለፉ ጀዋር መሃመድ ደግሞ ይቺ ለአምስተኛው ዙር የብጥበጣ ፕሮግራም ስኬት ታግዛለች በሚል ከንቱ ተስፋ በድብቅ ተቀርፆ የተላከልን ነው እስኪ እንኩና ተነሳሱ ሲል ለተከታዮቹ አቀረበ እንግዲህ ዛሬ ትናንት አይደለም https://www.youtube.com/watch?v=OmfkAqz3icQ&sns=fb

Miidhama lammiiwwan Sooriyaa

ምስል
Miidhamni lammiiwwan Sooriyaa ammas akkuma itti fufetti jira. Gareen shoroorkeessaan idila Addunyaa IS jedhamuudhaan beekamu ammoo du'aafi baqannaa lammiiwwan biyyattii irra ga'u daran hammeesseera. Balaa dhooyinsaa green kun har'a iddoowwan lamatti geessiseen lubbuun Namoota 78 darbeera. Balaa balleessanii baduu kanaan lubbuun Namootaa darbuun baay'ee gaddisiisaadha. Dabalata:

የሕግ ጥሰት ፈፅሞ ተጠያቂ አለመሆን አይቻልም

ይዋል ይደር እንጂ ማንኛውም ሕገ ወጥ ድርጊት ተጠያቂ ያደርጋል የሕግ ጥሰት በመፈፀም ከተጠያቂነት ያመለጠ ሰውና አካል የለም ነገር ግን ሕገ ወጥ ድርጊት የተፈፀመ ስለመሆኑ እንዳይታወቅ በሚደረገው ጥረት ተጠያቂነት ሊዘገይ ይችላል መቼም ቢሆን ተጠያቂነት ሊቀር እንደማይችል ግን መገንዘብ ጠቃሚ ነው ለምሳሌ በትንሹ እንይ ብንል  እንኳ ዶክተር ኢንጂነር እያለ በሃሰተኛ የማዕረግ ስም ብዙዎችን ሲያጭበረብር የቆየው ሳሙኤል ዘሚካኤል ጉዳዩ ለሕግ ቀርቦ ሲታይ ከቆየ በኃላ ተጠያቂ በመሆን የእስር ቅጣት ተወስኖበት የቅጣት ጊዜውን በማጠናቀቅ ከእስር እንደተለቀቀ ከሰሞኑ እየተሰማ ነው መቀጣት ለመታረም ነውና ሳሙኤል ዘሚካኤልም ከስህተቱ ተምሮ መልካም ዜጋ መሆን እንደሚችል አምናለሁ ሌባ ለአመሉ… እንዳይሆን እንጂ ልክ እንደሳሙኤል ሁሉ ሌላውም ግለሰብ፤መንግስታዊ አካልና ባለስልጣን የሕግ ጥሰት ፈፅሞ ተጠያቂ አለመሆን እንደማይችል በአገራችን ያለው ተመክሮ በማስረጃነት ሊቀርብ ሚችል ነው ባለፉት አመታት በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ብልሹ አሰራሮችን በመጠቀም የሕዝብና የመንግስትን ገንዘብና ንብረት የመዘበሩ ግለሰብ ባለስልጣናት ሕግ ፊት ቀርበው ፍርዳቸውን አግኝተዋል የፍርዳቸውን ቀን በመጠባበቅ ላይ የሚገኙም እንዳሉ ይታወቃል ዋና ኦዲተር አቶ ገመቹ ዱቢሶ ሰሞኑን ለተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት ሪፖርት፣ ብዛት ያላቸው የመንግሥት ተቋማት በተደጋጋሚ በየዓመቱ የሚሰጣቸውን አስተያየት ተግባራዊ በማድረግ ከማሻሻል ይልቅ፣ ወደባሰ ጥፋት እየገቡ መሆናቸውንና ለዚህም ዋና ምክንያቱ ተጠያቂ ያለመደረጋቸው መሆኑን ተናግረዋል እንግዲህ “አፍንጫ ሲመታ አይን ያለቅሳል” እንዲሉ ኢትዮጵያ ገንዘብና ንብረቱ በተለያዩ ምክንያቶች ተመዝብሮበት ዝም የሚል ሕዝብና መን

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አህመድ ናስር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡

ምስል
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አህመድ ናስር ከዚህ   ዓለም በሞት ተለዩ፡፡ የክልሉ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሃብታሙ ታየ ዛሬ እንዳስታወቁት አቶ አህመድ ናስር ከ2001 ዓ.ም. ጀምሮ ክልሉን በርዕሰ መስተዳድርነት መርተዋል ፡፡ የከልሉ ገዥው ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ህዝቦች ዴሞክራሲዊ ፓርቲ (ቤጉህዴፓ) በምክትል ሊቀመንበር መርተዋል፡፡ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ በእርሻ ምህንድስና፤ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በቻይና ሆሃ ዩኒቨርሲቲ በውሃ ምህንድስና የተከታተሉት አቶ አህመድ ናስር በአሁኑ ወቅት የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ሚኒስቴር በቀድሞው ግብርና ገጠር ልማት ሚኒስትር ዴኤታነት አገልግለዋል፡፡ የክልሉን ህዝብ ከድህነት ለማውጣት በተደረገው ጥረት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በቅንነትና በታማኝነት ሲያገለግሉ መቆያታቸውን ሃላፊው አመልክተዋል ፡፡ በተለይ ተበታትኖ የሚኖረውን የክልሉን ህዝብ በመንደር በማሰባሰብ ውጤታማ ለማድርግ በተደረገው የመጀመሪያው የክልሉ እድገትና ትረንስፎርሜሽን እቅድ እንዲሁም አሁን በመተግባር ላይ በሚገኘው ሁለተኛውን እቅድ ህይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድረስ በግንባር ቀደምትነት መርተዋል፡፡ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ብቻ ሳይሆን በደቡብ ክልል ሸበዲኖ እና ሃዋሳ ወረዳዎች በግብርና ባለሙያነት ሠርዋል፡፡ በ1957 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል ፈንታሌ ወረዳ ጠዴቻ መልካ ቀበሌ የተወለዱት አቶ አህመድ ናስር የክልሉን ህዝብ በክልል ምክር ቤትና በፌዴሬሽን ምክር ቤት ወክለው በቅንነት አገልግለዋል፡፡ ባደረባቸው ህመም በሀገር ውስጥና በውጪ ሀገር ህክምና ሲረዱ ቆይተው በ51 ዓመታቸው ትናንት ሌሊት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

“Abbaafi Haadha keenya irraa nyaannee Nama hin taanu”!

“Abbaafi Haadha keenya irraa nyaannee Nama hin taanu”! “Harree Ganama bade Galgala kur kuriin hin deebisu” jedha mammaaksi.Nama Naamusa hin qabneefi of ittummaadhaan ijjisaa jaame karaatti deebisuun baay’ee rakkisaa ta’a.”Itti himan malee itti hin hidhan”akkuma jedhamu Namoota Amala badaa qaban akka of sirreessaniif itti himuudhaaniifi gorsuudhaan  ala wanti ta’uu danda’u waan jiru natti hin fakkaatu. dubbisa dabalataa

ሂላሪ ክሊንተን ዴሞክራቶችን ለመወከል ከጫፍ መድረሳቸው እየተነገረ ነው

ምስል
በአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ የእጩዎች መረጣ ሂላሪ ክሊንተን ዴሞክራቶችን ለመወከል ከጫፍ መድረሳቸው እየተነገረ ነው።   ከቬርሞንቱ ሴናተር በርኒ ሳንደርስ ጋር እየተፎካከሩ ያሉት ሂላሪ ክሊንተን ትናንት ምሽት በተካሄደ ምርጫም በኬንታኪ በጠባብ ድምጽ ማሸነፍ ችለዋል። በኦሪገን ግዛት በተደረገ ሌላ ፉክክር ደግሞ በርኒ ሳንደርስ ማሸነፍ ችለዋል። ዴሞክራቶች አዛውንቱ ሳንደርስ መድረኩን ለሂላሪ ክሊንተን እንዲለቁ እየጠየቁ ነው፤ ሙሉ ትኩረታቸውን በምርጫ ቅስቀሳ ላይ እንዲያውሉት በሚል። ጠባብ የማሸነፍ እድላቸውን እንደሚሞክሩ የተናገሩት ሳንደርስ ግን እስከ ካሊፎርኒያው ምርጫ እንደሚወዳደሩ ገልጸዋል። ዴሞክራቶችን ለመወከል በእስካሁኑ ፉክክር፥ ሂላሪ ክሊንተን 2 ሺህ 291 ድምጽ ሲያገኙ በርኒ ሳንደርስ በ1 ሺህ 528 የድጋፍ ድምጽ ይከተላሉ። በሪፐብሊካኑ በኩል በእጩነት ለመቅረብ ድምጽ እያሰባሰቡ የሚገኙት ዶናልድ ትረምፕ ትናንት ምሽት በተካሄደው የኦሪገን ድምጽ አሰጣጥ ላይ አሸንፈዋል። ምንጭ፦ ቢቢሲ

Yaa`iin Liigii Dubartoota Dh.D.U.O 3ffaan har’a eegalameera

ምስል
Yaa`in dhaabbattummaa liigii dubartoota DhDUO 3ffaan har`a magaalaa Adaamaa Galma Abbaa Gadaatti gaggeefamaa oolera. Dura taa`aan Dh.D.U.O fi Preezidaantiin Mootummaa Naannoo Oromiyaa obbo Muktaar Kadir jalqaba yaa’ichaa irratti haasawa dhageessisaniin rakkoolee bulchiinsa gaarii hiikuu fi kiraa sassaabdummaa dhabamsiisuu keessatti ga’een dubartootarraa eegamu murteessadha jedhan. Hiyyummaa hir’isuu keessatti daran hirmaachuun guddina biyyattii ariifachiisuuf Dubartoonni hojjechuu akka qabanis dhaamaniiru. Dura teessuun liigii dubartoota Dh.D.U.O Aadde Qonjiit Baqqalaa gamsaaniitiin  liigichi yaa`ii kanaan murtee fi kallattii yaa'ii 2ffaa dabarserratti hundaa`uun hojiiwwan hanga ammaatti raawwatame qorachuun kallattii fula duraa kan kaa’u ta`a jedhaniiru. Yaa`in dhaabbattummaa liigii dubartoota Dh.D.U.O 3ffaan bakka gaggeessitoonni ol,aanaa dhaabichaa,liigiiwwan naannolee fi miseensonnii fi keessumoonni adda addaa argamanitti gaggeefamaa kan oole,borus itti fu

የ14 ፖለቲካ ፓርቲዎች ፈቃድ ተሰረዘ

ምስል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕጉና በመተዳደሪያ ደንባቸው መሠረት ማሟላት የሚገባቸውን ጉዳዮች እንዳላሟሉ የተረጋገጡ 14 የፖለቲካ ፓርቲዎች ፈቃድ መሰረዙን አስታወቀ። ቦርዱ በህገ መንግስቱ በተሻሻለው የኢትዮጵያ የምርጫ ህግ አዋጅ ቁጥር 532/1999 ዓ.ም እና በተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 573/2000 ዓ.ም መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመመዝገብ፣ እንቅስቃሴያቸውን የመከታተል፣ የመቆጣጠር፣ ድጋፍ የማድረግና ህጉን አሟልተው ባልተገኙ ጊዜ የመሠረዝ ሥልጣንና ኃላፊነት እንዳለው ተደንግጓል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንቅስቃሴ በመከታተልና በመቆጣጠር ሂደት ፓርቲዎች በህጉ የተቀመጡትን ድንጋጌዎች አሟልተው እንዲንቀሳቀሱ በተለያዩ ጊዜያት ከፖለቲካ ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራር ጋር የጋራ ምክክር ማድረጉን ቦርዱ አስታውሷል፡፡ በተጨማሪም ፓርቲዎቹ በህጉ መሠረት የሚጠበቅባቸውን ጉዳዮች ማሟላት እንዳለባቸው ተገቢውን ግንዛቤ እንዲጨብጡና ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ መጠነ ሰፊ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን መስራቱንም ነው የገለፀው፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ቦርዱ ህጉን ሳያሟሉ በተገኙና ማስተካከያ እንዲያደርጉ እገዛ ተደርጎላቸው ባላሟሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰድ እንዳለበት ይታወቃል፡፡ በዚህ መሠረት ቦርዱ በሕጉና በመተዳደሪያ ደንባቸው መሠረት ማሟላት የሚገባቸውን የሕግ ጉዳዮች ላላሟሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያላሟሏቸውን ድንጋጌዎችና አፈፃፀሞች በመዘርዘር በተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 573/2000 ዓ.ም እና በፓርቲዎቹ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት እርምጃ ለመውሰድ የሚገደድ መሆኑን አሳውቋል፡፡ ይሁን እንጂ ከዚህ የሚከተሉት 14 የፖለቲካ ፓርቲዎች እስከአሁን ድረስ በሕጉና በመተዳደሪያ ደ

ውሸት ያኮሰሰው ዶላር ሲቃርም

ምስል
ጀሌዎቹ ሲያንቆለጳጵሱት ፕሮፍ እያሉ ይጠሩታል የእነ ሲሳይ አጌና አይነቶቹ፤ በአሁኑ ወቅት የአርበኞች ግንቦት ሰባት አሸባሪ ድርጅት ሊቀመነበር እንደሆነ የሚነገርለት ብርሃኑ ነጋ ከሰሞኑ በደቡብ በኩል ታጣቂዎችን በማስረግ ያስገባነው እኛ ነን ኃላፊነቱንም እንወስዳለን ሲል የሃሰት ፕሮፓጋንዳውን ሲነፋ ተሰምቷል ይህም ኢህአዴግን በጭፍን   ከሚጠሉ የዲያስፖራ አባላት ጥቂት ዶላሮችን ለመቃረም ሊያግዘው እንደሚችል ይገመታል  እንኳን ኃላፊነት መውሰድ የሆነው ነገር ምን እንደሆነ የማወቅ መንገዱም ሆነ ብቃቱ የሌለው ይህ ሰው አፉን ሞልቶ በድፍረት በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች አለን ሲል ቱሪናፋውን ነፍቷል በአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ የአማርኛው ክፍል ጋዜጠኛ ታጣቂዎቻችሁ በየት አካባቢ ነው ያሉት ብሎ ላቀረበው ጥያቄ በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች አለን የሚል ድፍረት ተሞለበት ምላሽ አግኝቷል የኢትዮጵያ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትና የፌዴራል ፖሊስ የፀረ ሽብር የጋራ ግብረ ሃይል የኤርትራ መንግስት ተላላኪዎች ስማቸውን በመቀየር የኤርትራ የጉዞ ሰነድ ከተዘጋጀላቸው በኋላ ከአስመራ ተነስተው ወደ ኡጋንዳ በአውሮፕላን ቀጥሎም በተሽከርካሪ ወደ ኬኒያ ተጉዘው በሞያሌ በኩል ድንበር ተሻግረው በደቡብ ክልል በሚገኝ ጫካ ውስጥ ያልታወቁ መስሏቸው ራሳቸውን በመደበቅ መቆየታቸውን መግለፁ ይታወሳል። ግብረ ኃይሉ እንዳስታወቀው በዚያም ለተለያዩ የሽብር ተግባራት ሲዘጋጁ  በተካሄደው  ኦፕሬሽን ሚያዚያ 28 ቀን 2008 ዓመተ ምህረት በቁጥጥር ስር ውለዋል። በወቅቱ ለማምለጥ የሞከሩ ጥቂት አሸባሪዎችም ተገድለዋል። ይህን እውነት ሽምጥጥ አድርጎ የካደው ብርሃኑ ነጋ በአልሞት ባይ ተጋዳይነት ኃላፊነቱን ወስደናል፤በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ከኢትዮጵ

አሰልጣኝ ዶክተር ወልደመስቀል ኮስትሬ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ

ምስል
የቀድሞው የብሄራዊ አትሌቲክስ ቡድን አሰልጣኝ ዶክተር ወልደመስቀል ኮስትሬ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ *** ነፍስ ይማር*** ዶ/ር ወልደመስቀል ኮስትሬ ጥር 1939 ዓ ም በሰሜን ሸዋ ተጉለት እና ቡልጋ ተወለዱ። ዶ/ርወልደ መስቀል ኮስትሬ በ2 ዙር በመጀመሪያ ከ1964 -1970 እንደገና ደግሞ ከ1974 -1982 በአጠቃላይ 14 አመታትን በወጣትነታቸው ካሳለፉባት የምስራቅ አውሮፓዋ ሀገር ሀንጋሪ በባዮሎጂ ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ የዶክትሬት ዲግሪ ባለቤት ናቸው፡፡ ዶ/ር ወልደመስቀል ወደ ሀንጋሪ ለትምህርት ከማምራታቸው ከሳምንታት በፊት በ1964 በቶኪዮ ኦሎምፒክ ለሚሳተፈው የአትሌቲክስ ቡድናችን በ800 ሜ እና 1500 ሜትር ለተወዳዳሪነት ተመርጠው ነበር፡፡ ነገር ግን ትምህርት ይሻለኛል በማለት ውድድሩን በመተው ወደ ሀንጋሪ አምርተዋል፡፡ የአትሌቲክስ አሰልጣኝነትን የጀመሩት በኮተቤ ኮሌጅ አስተማሪ እያሉ በ70ዎቹ መጀመሪያ ላይ ሲሆን በ1972 የሙኒክ ኦሎምፒክ በሚሳተፈው ቡድናችን ውስጥ ዋና አሰልጣኝ ለነበሩት ንጉሴ ሮባ ምክትል አሰልጣኝ በመሆን ነበር፡፡ ዶክተር ወልደመስቀል በ1982 የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከተቀበሉ በኋላ ወደ ሀገራቸው ተመልሰው በስፖርት ኮሚሽን ውስጥ በከፍተኛ ባለሙያነት ሰርተዋል፡፡ ወደ አትሌቲክስ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝነት የመጡት የአሰልጣኝ ንጉሴ ሮባን ኅልፈት ተከትሎ በ1992 ነው፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ኢትዮጵያ ለዓለም ካበረከተቻቸው ምርጥ ምርጥ አትሌቶች ጀርባ እኝህ ኮስታራ አሰልጣኝ ይገኛሉ፡፡ ከ1992 የባርሴሎና እስከ 2008 ቤጂንግ ኦሎምፒክ ለ16 ዓመታት በዘለቀው የዋና አሰልጣኝነት ዘመናቸው ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ያኮሯትን የ5000 እና የ10,000 ሜትር አትሌቶች ለውጤት በማብቃት ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ዶ/ር ወ

የሽብር ተላላኪዎችን በቁጥጥር ስር የማዋሉ ስራ

ምስል
በቅርቡ የሽብር ተላላኪዎችን በቁጥጥር ስር የማዋሉ ስራ በአገር ውስጥ የዚህ ሀይል ተቀባይና ተባባሪን በመለየት ለመያዝ ባለመ መልኩ መከናወኑንና ይህም መሳካቱ ተገለፀ በቅርቡ የኤርትራ መንግስት አሰልጥኖ የላካቸው የሽብር ተላላኪዎችን በቁጥጥር ስር የማዋሉ ስራ በሀገር ውስጥ የዚህ ሀይል ተቀባይ እና ተባባሪን በመለየት በቁጥጥር ስር ለማዋል ባለመ መልኩ መከናወኑን እና ይህም በተሳካ ሁኔታ መፈፀሙን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትና የፌዴራል ፖሊስ የፀረ ሽብር የጋራ ግብረ ሃይል ገለፀ። አንድ የግብረ ሀይሉ የስራ ሀላፊ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮ ር ፖሬት እንደገለፁት ኦፕሬሽኑ የጥፋ ሀይሉን እንቅስቃሴ ከአስመራ ጀምሮ ከመከታተል ባለፈ ይህ ቡድን በአገር ውስጥ ያለውን ሰንሰለት ለመለየት እና በቁጥጥር ስር ለማዋል ታስቦ ተከናውኗል። ወደ አገር ውስጥ የገባው ሀይል ምንም ዓይነት የጦር መሳሪያ ሳይዝ መግባቱን ያነሱት ሀላፊው የዚህ ቡድን ተቀባይ ሀይሎች ግን ቀላል የጦር መሳሪያ እና ገጀራን የመሰሉ ድምጽ አልባ መሳሪያዎችን እንደታጠቁ መያዛቸውን ነው ያመለከቱት። በቁጥጥር ስር የዋሉት የሽብር ተላላኪዎች የሻዕብያ ተላላኪ የሆኑ እና በአገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ጸረ ሰላም ሀይሎች ተልዕኮን አስፈጻሚዎች መሆናቸውንም አስታውቀዋል። እነዚህን የሽብር ተላላኪዎች ቁጥር እና ዝርዝር ማንነታቸውን በተመለከተ ወደፊት ከምርመራ በል ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን ነው የገለፁት። የኤርትራ መንግስት ተላላኪዎች ስማቸውን በመቀየር የኤርትራ የጉዞ ሰነድ ከተዘጋጀላቸው በኋላ ከአስመራ ተነስተው ወደ ኡጋንዳ በአውሮፕላን ቀጥሎም በተሽከርካሪ ወደ ኬኒያ ተጉዘው በሞያሌ በኩል ድንበር ተሻግረው በደቡብ ክልል በሚገኝ ጫካ ውስጥ ያልታወቁ መስሏቸው ራሳቸውን

የኪራይ ሰብሳቢ ኃይሎች የበላይነት

ምስል
በአገራችን ኪራይ ሰብሳቢነት አደገኛ የጥፋት መንገድ እንደሆነ የሚያረጋግጡ አብነቶችን ለማቅረብ ብዙም አስቸጋሪ አይደለም ያስቸገራል ቢባል እንኳ ኪራይ ሰብሳቢነት ሕብረተሰብን ምን ያህል እንደሚያመሰቃቅል ከብዙ የአለማችን የከሸፉ መንግስታት ታሪክ በመነሳት ማረጋገጥ ይቻላል ሁለቱንም የታሪክ ማስረጃዎች   በማጣቀስ የኪራይ ሰብሳቢነትን ውጤት እንመልከት ከተባለ   በአገራችን ኪራይ ሰብሳቢነት መንግስታዊ ስልጣን ይዞ የነበረበትን የደርግ ስርዓት   ዋቢ ማድረግ ይቻላል  ደርግ ስልጣን ላይ ሲወጣ ይህ ነው የሚባል ሃብት ያልነበራቸው ወታደሮች ስልጣናቸውን በመጠቀም  ያልወረሱት የዜጎች ሃብት አልነበረም ቤቶችን፣ፋብሪካዎችን፣ባንኮችን፤ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን እንዲሁም መሬትን ወርሰዋል በዚህም ሳይወሰኑ ከእነሱ በስተቀር ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ሃብት በማፍራትና  በማበራከት ተግባር ውስጥ እንዳይገባ ከልክለዋል ይህ በተግባር ይተረጎም ይችል የነበረው የሕዝቡ ዴሞክራሲያዊ መብት ሲታፈን በመሆኑ ዴሞከራሲን ረግጠዋል የብሄሮችን ህልውና ክደው አሃዳዊ መንግስት እንደተጫነባቸው እንዲቀጥል አድርገዋል ነገር ግን ይህን በማድረጋቸው ለውጥ ፈላጊ የሆነውን የአገራችን ሕዝብ ተቃውሞ ቀስቅሰዋል በዚህ ምክንያት ለአስራ ሰባት ዓመታት  የተቀጣጠለው ጦርነት  አገሪቱን ከሞላ ጎደል የውድቀትና የመበታተን አፋፍ ላይ አድርሷት ነበር ይህ ኪራይ ሰብሳቢነት ለመንግስታዊ ስልጣን  ሲበቃ በማይቀር ሁኔታ የሚከሰት ውጤት  እንደሆነ የሚያረጋግጥ የራሳችን አገር ተመክሮ ነው በሌላ በኩል በሶማሊያ፤በሊቢያ፤በቡሩንዲ፤በደቡብ ሱዳን፤በኤርትራና  በመሳሰሉት የተከሰቱት የከሸፉና በመክሸፍ አቅጣጫ የሚጓዙ መንግስታት እዚሁ በቅርባችን የኪራይ ሰብሳቢነት የበላይነት ከሰፈነባቸው ስርዓቶች ጋር 

የሰቡት ዋጋቸው ውድ ነው፤ የጉፋያዎቹን ንገሩን

  አንዳንድ ተረት ካልተደጋገመ የሚሰማ የለም፡፡ ይሄንንም በድጋሚ አቅርበነዋል፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ትልቅ ዝሆን አንድ ትልቅ ገደል ውስጥ ወድቆ ይሞታል፡፡ ሌሊቱን የተራቡ ጅቦች ወደ ገደሉ አፋፍ መጥተው፣ ዞር ዞር ሲሉ ዝሆን እጅግ አዘቅት በሆነው ገደል ውስጥ ገብቶ መሞቱን አዩ፡፡ ከፊሎቹ ጅቦች፤ “እንዴት ግዙፍና የሰባ ዝሆን ነው?” ኧረ እንግባና የተራበ አንጀታችንን እናርስ!” አሉ፡፡ አንዳንድ ብልህ ጅቦች ግን፤ “ኧረ ጐበዝ! እጅግ ሩቅ ወደሆነው ወደዚህ ጉድጓድ ገብተን፤ ኋላ ሆዳችን ሲሞላ ተመልሰን ወደ ገደሉ አፋፍ መውጣት የማይሞከር ነገር ነው” አሉ፡፡ ብዙዎቹ ጅቦች፤ “እቺን ዳገት ብላችሁ ታወራላችሁ? ተደጋግፈን ፉት እንላታለን፡፡ ይልቅ በረሃብ ሳንሞት ቶሎ እንወስን” ጥቂቶቹ ጅቦች፤ “ኧረ ይሄ ገደል የዋዛ አደለም ጐበዝ! አንዴ ከገባን መመለሻም የለን” ብዙዎቹ ጅቦችም፤ “የምትጨቃጨቁን ከሆነ፤ ያለው መፍትሔ ድምጽ እንስጥና አብላጫውን ድምጽ ያገኘው አሸናፊ ይሁን!” ይሄው ዋናው የውሳኔ ሃሳብ ሆነና “ድምፅ ይሰጥ” ተባለ፡፡ ድምጽ ተሰጠ፡፡ “ወደ ገደሉ ገብተን የሞተውን ዝሆን እንብላና ረሃባችንን እንመክት!” ያሉት አሸነፉ፡፡ ጅቦቹ ሁሉ ተንደርድረው፣ ተግተልትለው፣ ወደ ገደሉ ገቡ፡፡ ያን ድልብ ዝሆን ተያያዙት፡፡ ጠገቡ፡፡ ለጥ ብለው ተኙ፡፡ ነጋ፡፡ የተረፈውን ተቀራመቱ፡፡ ቀናት እየገፉ ሲሄዱ የዝሆኑ ስጋ ተመናመነና አለቀ፡፡ ቀና ብለው የገደሉን ጫፍ አዩት፡፡ በጭራሽ የሚሞከር ነገር አይደለም፡፡ “ኧረ እንዴት ነው ይሄን ገደል የምንወጣው?”   አለ አንዱ ጅብ፡፡ ብዙዎቹ ጅቦች፤ “እስቲ ማታውን አድረን እናስብበትና ጠዋት መላ እንመታለን” አሉ፡፡ ነገም መጥቶ አፈጠጠ